የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት የእድሳት የጥገና ግንባታ አገልግሎት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት የእድሳት የጥገና ግንባታ አገልግሎት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
- ሎት 1. ኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ፣
- ሎት 2. ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፣
- ሎት 3. ሆሳዕና ቅርንጫፍ ፣
- ሎት 4. ዲላ ቅርንጫፍ ዲላ ፣
- ሎት 5. ቃሊቲ ቅርንጫፍ ፣
- ሎት 6. ሻሸመኔ ቅርንጫፍ ፣
ማንኛውም ተጫራች የኮንትራክተሮች ምዝገባ የምስክር ወረቀት (የታደስ የብቃት ማረጋገጫ) ያለውና
- ኮምቦልቻ ቅርንጫፍ የእድሳት ስራ GC/BC-6
- ድሬዳዋ ቅርንጫፍ የእድሳት ስራ GC/BC6
- ሆሳዕና ቅርንጫፍ የእድሳት ስራ GC/BC-7
- ዲላ ቅርንጫፍ የእድሳት ስራ GC/BC-7
- ቃሊቲ ቅርንጫፍ የእድሳት ስራ GC/BC-7 እና
- ሻሸመኔ ቅርንጫፍ የእድሳት ስራ GCBC-8 የሆነ ፣
በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የግብር ከፋይ ምዝገባ የምስክር ወረቀት እና በመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር የተመዘገቡበትን የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል መሆን አለበት። የአቅራቢዎች ዝርዝር ፣ እና ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በጨረታ ለመሳተፍ የተፈቀደለት /የክሊራንስ/ያለው፡፡ ለዚህ የተዘጋጀውን ዝርዝር የጨረታ ስነድ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል የድርጅቱ ግዥ ቡድን በግንባር በመቅረብ መግዛት ይችላሉ። ተጫራቾች ቴክኒካል እና ፋይናንሽያል ዶክመንቶችን ኦርጂናልና ኮፒ በተለያዩ በታሸገ ኤንቨሎፕ እንዲያቀርቡ እናሳስባለን።
ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ4፡30 ሰዓት ይከፈታል። ነገር ግን 11ኛው ቀን የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው ስራ ቀን ይከፈታል። ተጫራቾች ለሚጫረቱበት የእድሳት ስራ አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶች ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡
የጨረታ ማስከበሪያ በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት (Ethiopian Industrial lnputs Development Enterprise) ስም ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና
- ለሎት 1 ብር 105,000.00 (አንድ መቶ አምስት ሺህ) ፣
- ለሎት 2 ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ) ፣
- ለሎት 3- ብር 40,000.00 (አርባ ሺህ) ፣
- ለሎት 4 ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ) ፣
- ለሎት 5- ብር 90,000.00 (ዘጠና ሺህ) እና
- ለሎት 6 ብር 10,000.00 (አስር ሺህ) ከጨረታው ቴክኒካል ስነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡- አዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ፒያሳ ከከሊፋ ህንፃ በስተሰሜን የባቡር ሀዲዱን ተሻግሮ ወደ አራት መንታ በሚወስደው መንገድ ጣሊያን ሰፈር (የቀድሞ ጅንአድ) ቢሮ)።
ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ፡-
ስልክ ቁጥር 0111-57-24-97 ይደውሉ ወይም በአካል መጎብኘት ይችላሉ።
