የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የወረዳ 4 ፋይናንስ ፅ/ቤት ለሰራተኞች አገልግሎት የሚውሉ የፅዳት እቃዎች፣ የደንብ ልብስ፣ የቢሮ አላቂ እቃዎች፣ የቢሮ ቋሚ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
1ኛ ዙር ግልፅ ጥቅል ጨረታ ማስታወቂያ
የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የወረዳ 4 ፋይናንስ ፅ/ቤት ለሰራተኞች አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች የተገለፀዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
- ሀ. የፅዳት እቃዎች
- ለ. የደንብ ልብስ
- ሐ. የቢሮ አላቂ እቃዎች
- መ. የቢሮ ቋሚ እቃዎች
በዚህም መሰረት መወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ህጋዊ ተጫራች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶችማሟላት ይኖርባቸዋል።
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ሥራ ፍቃድ ያላቸውና ከአገር ውስጥ ገቢ ባለስልጣን የዘመኑን የመንግስትግብር የከፈሉ መሆኑን ከግብር እዳ ነፃ መሆኑን የሚያረጋግጥ ሰነድ ማቅረብ የሚችል
- የአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡበትን የምስክር ሰርተፍኬት ኮፒ ማቅረብ የሚችሉ መሆናቸውንእና የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ እንዲሁም የግብር ከፋዮች መለያ ቁጥር ኮፒ ሰርተፍኬት አያይዘውማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር ብር/ በመክፈል ይህ የጨረታ ማስታወቂያከመጣበት ባሉት 15 የስራ ተከታታይ ቀናት ከ2፡30-11፡30 ሰአት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ፋይናንስ ፅ/ቤት 1ኛ ፎቅ ሳዶ ቢሮ ቁጥር 101 የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
- የጨረታ ማስከበሪያ ከሚጫረቱት ጠቅላላ ዋጋ 2% (ሁለት ፐርሰንት) እና ከዚያ በላይ በባንክየተመሰከረለት (C.P.O) ማስያዝ ይኖርበታል።
- የጨረታ አሸናፊ እንደሆኑ ከተለየ በኋላ አሸናፊዎች ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% (አስር ፐርሰንት) የውልማስከበሪያ በባንክ የተመሰከረለት (C.P.O) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የሚወዳደረበትን ዋጋ በታሸገ ኢንቨሎፕ ዋናውን እና ኮፒውን ጨረታው ከወጣበት ቀንጀምሮ እስከ 15 (አስራ አምስት) የስራ ቀናት በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት እቃ ናሙና ጨረታው ከመከፈቱ ከሁለት ቀናት በፊት ማቅረብ ግዴታይኖርባቸዋል
- ጨረታው በ16ኛው ቀን ከጠዋት 3:00 ሰአት ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸውበተገኙበት ወይም ባልተገኙበት ከጠዋቱ 4፡30 በወረዳ 04 ፋይናንስ ፅ/ቤት የሚከፈት ሲሆን የበአልቀን ከሆነ በሚቀጥለው ቀን ይሆናል።
- ለጨረታው የሚቀርቡት እቃዎች የጥራት ደረጃቸውን የጠበቁ መሆን አለባቸው
- ማንኛውም ተጫራች በሚያቀርበው እቃ ናሙና ላይ የተለየ ምልክት ወይም የድርጅቱን ማህተም ማድረግየተከለከለ ነው እንዲሁም ከ አንድ (1) በላይ ሳምፕል አስገብቶ ቢገኝ ከውድድር ውጪ እንደሚሆኑእናሳውቃለን፡፡ ማንኛውም ተጫራች ማህተሙን የሚጠቀመው በወረቀት ላይ ማህተም በማድረግ እቃውላይ በፕላስተር በመለጠፍ ብቻ ነው
- ማንኛውም ተጫራች በግዢ ጨረታው ላይ ከተጠየቀው ውጪ ናሙና ማቅረብ ከውድድር ውጪያደርጋል።
- ማንኛውም አቅራቢ የሚሞላው ሰነድ ላይ ስርዝ ድልዝ ካለው ወይም ለማንበብ አስቸጋሪ ሆኖ ከተገኘከውድድር ውጪ ይሆናል።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ 0955 373 636 በመደወል ማግኘት ይቻላል።
-facebook page Akaki kality woreda 4 communication
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ፋይናንስ ፅ/ቤት
