ፈያ ኢንተግሬትድ ዲቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን ለ 2017 ዓ.ም የትምህርት ቤት ዩኒፎርም ማሰፋት እና መግዛት ይፈልጋል
ፈያ ኢንትግሬትድ ዲቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን
ድርጅታችን ፈያ ኢንተርግሬትድ ደቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን መንግስታዊ ያልሆነ አገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን ላለፉት 21 ዓመታት በሀገሪቱ በተለያዩ ክልሎች ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ የበጎ አድራጎት ስራዎችን ከመንግስትና አለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን እየሰራ ያለ ህጋዊ የኢትዮጵያ ነዋሪዎች በጎ-አድራጎት ድርጅት ነው::
አሁን ከUNOCHA/EHF ባገኘነው “Emergency life-saving health response for cholera outbreak in West Guji zone, Oromic region, Ethiopia" ድርጅታችን ከዚህ በታች የተገለጹትን አላቂ እቃዎችን በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
|
ተ/ቁ |
የእቃው አይነት |
ብዛት |
|
1 |
የልብስ ሳሙና 250 ግራም ጠንካራ በቀላሉ የማይርስ መሸፈኛ ያለውና የአገልግሎት ዘመን የተፃፈበት (Laundry soap 250 gm, hard water resistant & package with labeled expiry date |
11,871 |
|
2 |
የገላ ሳሙና 100 ግራም ጠንካራ በቀላሉ የማይርስ መሸፈኛ ያለውና የአገልግሎት ዘመን የተፃፈበት (Body soap 100gm, hard water resistant & package with labeled expiry date) |
11,871 |
ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያማሉ ተጫራቾች በከፊል ወይም በሙሉ መጫረት ይችላሉ።
- በመስኩ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገበበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
- ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ለሁሉም አጠቃላይ ዋጋ 2% (ፐርሰንት) በድርጅታችን (ፈያ ኢንተግሬትድ ዲቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን) ስም በባንክ የተረጋገጠ (ሲፒኦ) ብቻ ማቅረብ አለባቸው ከሚቀርበው አጠቃላይ ዋጋ 2% (ፐርሰንት) በታች ያስያዘ ከጨረታው ዉድድር ውጪ የሚደረግ ይሆናል።
- ስለጨረታ የሚገልጸውን ሰነድ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ) በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት ጨረታው በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሰባት (7) የሥራ ቀናት ከፈያ ኢንትግሬትድ ዲቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን ዋናው መስሪያ ቤት በመምጣት መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ ሰኔ 14 2015 ዓ.ም. እስከ 8፡30 ሰዓት ድረስ በመምጣት ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ሰኔ 14 ቀን 2015 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ታሽጎ ከቀኑ 8፡45 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ተጫራቾች ማቅረብ የሚገባቸውን የጨረታ ናሙና ጨረታው በሚከፈትበት ቀን ብቻ ይዘው መምጣት/ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-557-8114 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
- ድርጅታችን የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- አሸናፊው ተጫራች ባሸነፈበት ዋጋ ያሸነፈበትን የእቃ ዝርዝር ውል በገባ ማግስት ማቅረብ ይጠበቅበታል።
- ለተሸናፊ ተጫሪቾች ለጨረታው ማስረከቢያ ያስያዙት ሲፒኦ እና ናሙና ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል።
ፈያ ኢንተርግሬትድ ደቨሎፕመንት ኦርጋንይዜሽን
አድራሻ ሜክሲኮ ቀይ መስቀል አ.አ ቅርንጫፍ ፊት ለፊት ከባልቻ
ሆስፒታል ጀርባ ኢትዮ ካናዳ ክሊኒክ አጠገብ
+25111 557 8114
