የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ የበቆሎ ኮምባይን ሀርቨስተር ማሽን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመከራየት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ቁጥር ጣበስፋ /ብግጨ /01/217
የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ የበቆሎ ኮምባይን ሀርቨስተር ማሽን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመከራየት ይፈልጋል።
የማሽኑ ዓይነት:-
- ማሽኑ በራሱ የሚሰበስብ የሚሸለቅቅና የሚፈለፍል፣
- ምርቱን በራሱ መገልበጥ የሚችል፡
- ማሽኑ በቀን አጭዶ የመውቃት አቅሙ ከ20 ሄ/ር በላደ የሆነ፣
- ማሽኑ ምርት የመሸከም አቅሙ ከ22 ከ/ስ በላይ የሆነ፣
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ብቁ ተጫራቾች ህጋዊ የ2016/2017 ዓ.ም. የታደሰ የንግድ ፈቃድ የዘመኑን ግብር መክፈላቸውን የሚያረጋግጥ ከግብር ሰብሳቢው ባለስልጣን የተሰጠ የታክስ ክሊራንስና በጨረታ መሳተፍ የሚያስችል የድጋፍ ደብዳቤ/ የምስከር ወረቀት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር፣ ለተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት በተጨማሪም ተጫራቾች የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ወይም ሌላ አግባብነት ያለው አካል ባዘጋጀው የዕቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ መካተታቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው::
- ጨረታው ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ላይ ይዘጋል፡፡ ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ጨረታው ከመዘጋቱ በፊት ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በጨረታው መከፈቻ ላይ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከታች በቁጥር 4 ላይ በተገለፀው አድራሻ ጥቅምት 24 ቀን 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ላይ ይከፈታል፡፡ ዘግይቶ የሚቀርብ የመጫረቻ ሰነድ ውድቅ ይደረጋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 300.00 /ሦስት መቶ/ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቁጥር 1000057735167 በመክፈልና የባንከ አድቫይስ በማቅረብ በተራ ቁ.4 ከተመለከተው ቢሮ እና በተጨማሪም ባህር ዳር ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ከርስቲያን ፊት ለፊት በሚገኘው ማስተባበሪያ ቢሮ መግዛት ይችላሉ።
- የጨረታው ማስረከቢያና መከፈቻ አድራሻ ቀጥሎ የተመለከተው ነው፡፡
ጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ ማስተባበሪያ ቢሮ
ካዛንቺስ ከመናኸሪያ ሆቴል ወደ አቧሬ አቅጣጫ በሚወስደው አስፋልት መንገድ
ከጨርጨር ስጋ ቤት ዝቅ በማለት
የቀድሞው ተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ ግቢ ውስጥ
ስልክ ቁጥር 011 5-586725
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን 2% ብር በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ሰነድ ሲፒኦ (CPO) ወይም በሁኔታዎች ላይ ባልተመሠረተ የባንከ ዋስትና /ጋራንቲ/ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ጨረታው ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለ60 ቀናት ነው::
- የጨረታው ማስከበሪያ ዋስትና ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለ90 ቀናት ነው::
- ፋብሪካው ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ለበለጠ መረጃ በስልከ ቁጥር 011 5-586225 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
ጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ
