በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ለድርጅቱ አገልግሎት የሚውሉ የእሳት ማጥፊያ መሳሪያዎች ጥገናና እድሳት፣ ሙሌት ባለሞያዎች /ድርጅቶች ለ2 /ሁለት/ አመት በኮንትራት በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል ፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር አ.መ.ኬሩ 001/2017
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ለድርጅቱ አገልግሎት የሚውሉ የእሳት ማጥፊያ መሳሪያዎች ጥገናና እድሳት፣ ሙሌት ባለሞያዎች /ድርጅቶች ለ2 /ሁለት/ አመት በኮንትራት በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል ፡፡ አስፈላጊው ዝርዝር በጨረታ ሰነዱ ተቀምጧል፡፡
- ማንኛውም ብቁ የሆነ ተጫራች የ2017 ዓ.ም ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀትና ቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
- ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰአት ከአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ዋና መ/ቤት እና በአዲስ አበባ ሳሪስ አቦ መርቲ ህንፃ በሚገኘው ቅርንጫፍ መ/ቤት የማይመለስ 200.00 /ሁለት መቶ/ ብር በመክፈል መግዛት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የቀረበውን ዋጋ 2% በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል። ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ቴከኒካልና ፋይናንሻል ኦፈር ኦርጅናልና ኮፒ ለየብቻ በማሸግ እስከ ጥቅምት 28/2017 ዓ.ም በአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ዋና መስሪያ ቤት ከአዳማ 15 ኪ.ሜ ወደ አሰላ በሚወስደው አስፋልት ዳር ባለው የፋብሪካው ግቢ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው ጥቅምት 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡00 ሰዓት ተዘግቶ ቴከኒካል ኦፈሩ ብቻ በዕለቱ ጥቅምት 28 ቀን 2017 ዓ.ም 5፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ዋናው መ/ቤት አዳራሽ ውስጥ ይከፈታል፡፡ የፋይናንሻል ኦፈሩ መክፈቻ ቀን በቴክኒካል መክፈቻው እለት የሚገለጽ ይሆናል፡፡
- ድርጅቱ/ፋብሪካው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ አድራሻ
ስልክ:- 0920935336/0222250266
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን
የአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ
