በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት የልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡- የመ/ል/ድ/አስ/ባለ/ግልጽ ጨረታ 01/2017
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት የልማት ድርጅት አስተዳደር ባለስልጣን የእቃና አገልግሎት ግዥ የጨረታ ማስታወቂያ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት የልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። ስለሆነም፡-
ሎት 1 ---------------- የሆቴል አገልግሎት፣
ሎት 2 ---------------- ህትመት፣
ሎት 3 ---------------- ቋሚ የቢሮ እቃዎች ፈርኒቸር ፣ ኤሌክትሮኒከስ እና ሌሎችም፣
ሎት 4 ---------------- የታሸገ ውሃ፣
ሎት 5 ---------------- አላቂ የቢሮ እቃዎች እና የፕሪንተር ቀለም፣
ሎት 6 ---------------- የተሽከርካሪ የወንበር ልብስ፤ ኩሽን፤ የተሽከርካሪ ቴፕ ሪሞት
ኮንትሮል እና ሌሎችም
♦ ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆን አለባቸው።
♦ የተጫራቾች በፋይናንስ ቢሮ ዌብሳይት ላይ በአቅራቢዎች ሊስት ላይ የተመዘገቡ መሆን አለባቸው፡፡
♦ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በ CPO ማስያዝ አለባቸው፡፡
ሎት 1 --------- ብር 10,000.00 /አስር ሺህ ብር/፣
ሎት 2 --------- ብር 1,000.00 /አንድ ሺህ ብር/፣
ሎት 3 --------- ብር 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/፣
ሎት 4 --------- ብር 5,000.00 /አምስት ሺህ ብር/፣
ሎት 5 --------- ብር 3,000.00 /ሶስት ሺህ ብር/፣
ሎት 6 --------- ብር 3,000.00 /ሶስት ሺህ ብር/፣
♦ ተጫራቾች የቫት ተመዝጋቢ ሆነው ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉና መለያ ቁጥር /ቲን ነምበር/ ያላቸው መሆን አለባቸው።
● የጨረታ አሸናፊ አሸናፊነቱን ሲገለፅለት ያሸነፈበትን ከጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ በCPO ማስያዝ አለባቸው።
♦ ተጫራቾች ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ፒያሳ ከሚገኘው ዋስትና የንግድ ማእከል ህንፃ 8ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 8/03 የግዥና ንብረት አስተዳደር ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ቢሮ በመቅረብ በ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ድረስ የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።
• ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ዋናውን እና ኮፒ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማደረግ የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 11ኛው የስራ ቀን 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
♦ ጨረታው የሚዘጋበት ቀን የጨረታ ማስታወቂያው በወጣ በ11ኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጐ በዚሁ ቀን ጠዋት 4፡15 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ወይም በሌሉበት በመ/ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ 4ኛ ፎቅ ይከፈታል።
● መስሪያ ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ይሁን ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
● ዘግይቶ የመጣ የጨረታ ፖስታ ተቀባይነት የለውም።
አድራሻ
ፒያሳ ከሚገኘው ዋስትና የንግድ ማዕከል ህንፃ 8ኛ ፎቅ
የግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡-251-1-11-12-51-48
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት የልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን
