በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን መ/ቤት በ2017 በጀት አመት ከመደበኛ በጀት አመታዊ ማሽነሪዎች እና የተሽከርካሪዎች ጥገና አገልግሎት ግዢ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን መ/ቤት በ2017 በጀት አመት ከመደበኛ በጀት አመታዊ ማሽነሪዎች እና የተሽከርካሪዎች ጥገና አገልግሎት ግዢ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት የምትችሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- በዘመኑና በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸው፤
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN NO) ያላቸው እና የተጨማሪ እሴት ታከስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-2 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች በአካባቢያችን /በኮምቦልቻ ከተማ/ ጋራዥ /ቅርንጫፍ ጋራዥ/ ስለመኖሩ መረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
- ጨረታው ጸንቶ የሚቆይበት ጊዜ የጨረታ ሰነዱ ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለ40 ቀናት ሲሆን ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (BID BOND) ብር የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ 2% በማስላት በባንከ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዢያ (CPO) በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ ማቅረብ አለበት፡፡
- ማንኛውም ተጫራች መ/ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሰነድ በሚጠይቀው የዋጋ አሞላል ብቻ መሙላት አለበት፡፡ በሚጠይቀው ዋጋ አሞላል ካልሞሉ የጨረታ ሰነዱ ውድቅ ይሆናል፡፡
- የጨረታው ውድድር የሚካሄደው በሎት /በጥቅል/ ድምር ውጤት ስለሆነ የማይሞላ አይተም መኖር የለበትም፡፡ ያልተሞላ አይተም ከተገኘ ከጨረታው ውድቅ ይሆናሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) ለእያንዳንዱ ሎት በመክፈል ከግ/ፋይ/ን/አስ/ደ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 508 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው አየር ላይ የሚቆየው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 24/02/2017 ዓ.ም እስከ 08/03/2017 ዓ.ም 11፡30 ሰዓት ድረስ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆነ አንድ ቅጂ ማለትም ዋናና ቅጂ በማለት ለየብቻ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ መንገዶች ባለስልጣን መ/ቤት በግዥና/ፋይ/ን/አስ/ደ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 508 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ 09/03/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥና ፋይ/ን አስ/ደ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 508 በ09/03/2017 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በ 4፡30 ሰዓት ላይ ይከፈታል፡፡ ነገር ግን ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ቅዳሜ፣ እሁድና የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት መሆኑን እንገልጻልን፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለበለጠ መረጃ በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን መ/ቤት በአካል በመቅረብ ወይም በስልከ ቁጥር 033-3-51-33-37/ 033-5-51-05-04 መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- ማሳሰቢያ፡- የመስሪያ ቤቱ አድራሻ ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ህንጻ አምስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 508 ላይ ነው፡፡
በአብክመ የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር
መንገዶች ባስስልጣን መ/ቤት
