በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሻሸመኔ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በዲስትሪክቱ ለሚከናወኑ የተለያዩ የግንባታ ሥራዎች አገልግሎት የሚሰጡ የስሪት ዘመናቸው እ.ኤ.አ ከ2007 ዓ.ም ወዲህ የሆነ የጭነት መጠናቸው 16 ሜ/ኩ የሆነ 7 ገልባጭ መኪኖችን ለጎባ ደሎመና መንገድ ጥገና ሥራ እንዲሁም ዊል ኤክስካቫተር ብዛት 2 ለዶዶላ ሰብስቤ ዋሻ መንገድ ጥገና ሥራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ተከራይቶ ማሠራት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ኢመአ ሻሸ/ዲ/001/2017
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሻሸመኔ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በዲስትሪክቱ ለሚከናወኑ የተለያዩ የግንባታ ሥራዎች አገልግሎት የሚሰጡ የስሪት ዘመናቸው እ.ኤ.አ ከ2007 ዓ.ም ወዲህ የሆነ የጭነት መጠናቸው 16 ሜ/ኩ የሆነ 7 ገልባጭ መኪኖችን ለጎባ ደሎመና መንገድ ጥገና ሥራ እንዲሁም ዊል ኤክስካቫተር ብዛት 2 ለዶዶላ ሰብስቤ ዋሻ መንገድ ጥገና ሥራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ተከራይቶ ማሠራት ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሠረት ፡-
በመንግስት የግዢና ንብረት አስተዳደር መመሪያ መሠረት በንግድ ዘርፉ የተሰማሩ፣ የግብር ግዴታቸውን የተወጡ እና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ የሀገር ውስጥ ተወዳዳሪዎችን በጨረታው እንዲሳተፉ ይጋብዛል
- በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን ሻሸመኔ በዲስትሪክቱ የግዢ አቅ/ ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ የማይመለስ የኢትዮጵያ ብር 200.00 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000002579859 ገቢ በማድረግ ገቢ ያደረጉበትን ሠነድ በመያዝና በማቅረብ የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- በጨረታው ለመሳተፍ የባለቤትነት መታወቂያ ደብተር (ሊብሬ) ወይንም ህጋዊ ውክልና ያላቸው መሆንና ሰነዱን ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይገባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000.00 በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ስም በባንክ በተረጋገጠ ሲፒአ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ማሸነሪዎቹን እንዲያስገቡ በተነገራቸው በ5 የሥራ ቀናት ውስጥ ማሰማራት የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ለሚያቀርቧቸው ማሽነሪዎቹ ሙሉ የመድን ዋስትና የተገባላቸውና የሚንቀሳቀሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ዝርዝር የጨረታ ሁኔታዎችን ከጨረታ ሠነዱ ላይ ያገኙታል፡፡
- ጨረታው ሻሸመኔ በሚገኘው የዲስትሪክቱ የስብሰባ አዳራሽ በጨረታ ሠነዱ ላይ በተገለፀው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ዕለት ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ከጠዋቱ 4፡15 ይከፈታል።
- ዲስትሪከቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
* ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 046 211 4616 ወይም 046 110 2730 ዘወትር በሥራ ሰዓት መጠቀም ይቻላል።
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሻሸመኔ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት
