በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ በጨረታ ሰነዱ ላይ በዝርዝር የተገለጹትን የእሳት አደጋ መከላከያ ኬሚካሎች ሙሌትና ጥገና በጨረታ አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል፡፡
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 002/2017
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ በጨረታ ሰነዱ ላይ በዝርዝር የተገለጹትን የእሳት አደጋ መከላከያ ኬሚካሎች ሙሌትና ጥገና በጨረታ አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ፡-
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዶችን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት በአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ዋና መ/ቤት ወይም አዲስ አበባ በሚገኘው ቅርንጫፍ ቢሮ ሳሪስ አቦ መርቲ ህንፃ የማይመለስ 100.00/ አንድ መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፈቃድ የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆኑን የሚገልጽ ማስረጃ የቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልጽ ኮፒውን ከእጅ ዋጋ ጋር በፖስታ አሽጎ ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የድርጅታቸውን ሙሉ ስምና አድራሻ በሚያቀርቡት የጨረታ ሰነዳቸው ላይ አሟልተው መጻፍ ያለባቸው ሲሆን በሰነዱም ላይ ፊርማና ማህተም መኖር አለበት፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ ዋጋ ብር 50,000.00 /ሃምሳ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ማያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው የሰነድ ሽያጭ ባበቃበት በመጨረሻው 11ኛው ቀን በአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ቅጥር ግቢ በፋብሪካው አዳራሽ ውስጥ በ5፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያው ቀን በ5፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ /ከአዳማ ወደ አሰላ በሚወስደው አስፋልት መንገድ ዳር ከአዳማ 15 ኪ.ሜ/
- ፋብሪካው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለተጨማሪ መረጃ አድራሻ ፡
ስልክ ቁጥር፡- 0920935336 ወይም ሞባይል 0911651515
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ
