Tender Detail

Tender Details

  • Company Amhara Pipe Factory (APF) (የአማራ ፓይፕ ፋብሪካ ኃላ/የተ/የግል ማህበር)
  • Address ባህር ዳር ከተማ ፡ አማራ ክልል ፡ ኢትዯጵያ, Phone: 09-35-98-37-29
  • Websitehttps://www.amharapipe.et/
  • Deadline26 Dec 2024, 2:00 PM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date
  • Categories Industry And Factory

የአማራ ፓይፕ ፋብሪካ ኃላ/የተ/የግል ኩባንያ ከዚህ በታች በሎት የተዘረዘሩትን ተረፈ ምርቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል::


የተረፈ ምርት ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር፡- /08/2017

 

የአማራ ፓይፕ ፋብሪካ ኃላ/የተ/የግል ኩባንያ ከዚህ በታች በሎት የተዘረዘሩትን ተረፈ ምርቶች ማለትም፡-

ሎት 1 -  የፕላስቲከ ከረጢቶች

ሎት 2 - ስስ ፌስታሎች

ሎት 3 - የፕላስቲክ ፓሌት ጣውላ

ሎት 4 - የእንጨት ፓሌት ጣውላ

ሎት 5 - የካኪ ከረጢቶች

ሎት 6 - የፒፒአር ፓይፕ

ሎት 7 - የፍላት ሆዝ ፓይፕ

ሎት 8 - የዩፒቨሲ ፓይፕ ራቨር ሲሎችን እና

ሎት 9 - Green house sheet እና common plastic sheet ተረፈ ምርት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል:: ስለሆነም ከዚህ በታች የተገለፁትን የጨረታ መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ (መወዳደር) ይችላሉ፡፡

  1. ተረፈ ምርቶችን መግዛት የሚፈልግ ማንኛውም ግለሰብ ወይም ድርጅት የንግድ ፈቃድ እና ሌሎች የሕጋዊነት ሠነዶችን ማቅረብ ሳይጠበቅበት በጨረታው መሳተፍ ይችላል፡፡
  2. ተወዳዳሪዎች የጨረታ ማስከበሪያ ለእያንዳንዱ ሎት ብር 5,000.00 (አምስት ሺህ ብር) በጥሬ ገንዘብ ወይም ከባንክ በፋብሪካው ስም በተዘጋጀ CPO ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ጋራንቲ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል ከፋብሪካው ገንዘብ ያዥ አንደኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 103 መግዛት ወይም በኢ-ሜይል (e-mail) አድራሻ amharapipefactory@gmail.com ማግኘት ይችላሉ፡፡
  4. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ዋጋቸውን የጨረታ ማስከበሪያ እና ሌሎችን ማስረጃዎች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ቢሮ ቁጥር 206 ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው::
  5. ጨረታው 16ኛው ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 206 ከቀኑ 800 ላይ ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከቀኑ 830 ላይ የሚከፈት ይሆናል፡፡
  6. 16ኛው ቀን ሕዝባዊ በዓል ወይም የእረፍት ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓትና ቦታ ተዘግቶ የሚከፈት ይሆናል፡፡
  7. ተጫራቾች የሚሸጡት ተረፈ ምርቶችን በአካል በፋብሪካው አድራሻ በመቅረብ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከጠዋቱ 400-500 ማየት ይችላሉ፡፡
  8. ፋብሪካው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

        ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- 0935-98-37-29/09-18-08-18-26 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

 

የአማራ ፓይፕ ፋብሪ/የተ/የግል ማህበር

Save Tender