የኢካፍኮ አክሲዮን ማህበር የችፕውድ ማምረቻ ማሽኖችን ከነመለዋወጫዎቹ የስታይሮፖር ምርት ማምረቻ ማሽኖችን ባሉት ሁኔታ በቦታው ላይ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር 007/2017
የኢካፍኮ አክሲዮን ማህበር የችፕውድ ማምረቻ ማሽኖችን ከነመለዋወጫዎቹ የስታይሮፖር ምርት ማምረቻ ማሽኖችን ባሉት ሁኔታ በቦታው ላይ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ በጨረታው ለመወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ፤
- ደብረዘይት መንገድ ሳሪስ ከሚገኘው የድርጅቱ ሽያጭ ከፍል በመቅረብ የማይመለስ ብር 1000.00 /አንድ ሺህ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሠነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ሠነዱን መግዛት የሚቻለው ዘወትር በሥራ ቀን ከጠዋቱ 2፡00 - 6፡00 እና ከሰዓት በኋላ ከ7:00 -10፡00 ሰዓት ብቻ ነው::
- ተጫራቾች የማሽኖቹን ሁኔታ እስከ ጨረታው መዝጊያ ጊዜ በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡00- 10፡30 ድረስ በፋብሪካው ውስጥ በአካል ተገኝተው ማየት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ድርጅቱ ለጨረታ ባዘጋጀው ሳጥን ውስጥ መስገባት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ያቀረቡትን የመወዳደሪያ ጠቅላላ ዋጋ 10% የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ CPO በማዘጋጀት ከዋጋ ማቅረቢያው ኤንቨሎፕ ውስጥ ተካቶ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ጨረታው ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0911 86-27-92 /0911 96-09-51 በመደወል መረዳት ይቻላል፡፡
ኢካፍኮ አክሲዮን ማህበር
