በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ለአቡነ ባስልዮስ የቅ/የመ/ጀ/ደ/ት/ቤት ለ2017 ዓ.ም የስራ ዘመን የደንብ ልብስ ፣ የፅህፈት መሳሪያዎች ፣ የህንፃ ቁሳቁስ እና ተገጣጣሚ እቃዎች ፣ ፕላን ማሽነሪ እቃዎች ፣ መሰረት ልማት ስራዎችና የህንፃ ቁሳቁስ እና ተገጣጣሚ እድሳት ጥገና በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛትና ለማሰራት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የግዥ መለያ ቁጥር፡- 2ኛ ዙር ጨረታ 002/2017
በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ለአቡነ ባስልዮስ የቅ/የመ/ጀ/ደ/ት/ቤት ለ2017 ዓ.ም የስራ ዘመን የደንብ ልብስ ፣ የፅህፈት መሳሪያዎች ፣ የህንፃ ቁሳቁስ እና ተገጣጣሚ እቃዎች ፣ ፕላን ማሽነሪ እቃዎች ፣ መሰረት ልማት ስራዎችና የህንፃ ቁሳቁስ እና ተገጣጣሚ እድሳት ጥገና በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛትና ለማሰራት ይፈልጋል።
|
ሎት |
የእቃው አይነት |
|
ሎት 1 |
የደንብ ልብስ |
|
ሎት 2 |
አላቂ የትምህርት መሳሪያዎች |
|
ሎት 3 |
ፕላን ማሽነሪ እቃዎች |
|
ሎት 4 |
ህንፃ ቁሳቁስ እና ተገጣጣሚ እቃዎች |
|
ሎት 5 |
መሰረተ ልማት ስራዎች |
|
ሎት 6 |
የህንፃ ቁሳቁስ ተገጣጣሚ እድሳት ጥገና |
በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተገለፁትን መስፈርቶች አሟልተው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው እና የዘመኑን ግብር ለመክፈላቸው ማስረጃ የሚያቀርቡ፤
- በገንዘብ እና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር (በመንግስት ግዥ ኤጀንሲ ድረ-ገፅ ላይ የተመዘገቡበትን የአቅራቢነት ኮፒ)፤ በጨረታው ለመሳተፍ የሚችሉ መሆኑን ከኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ወይም ጉዳዩ ከሚመለከተው አካላት የድጋፍ ደብዳቤ የሚያቀርቡ፤
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን የምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው፡፡ በጨረታው ለመሳተፍ ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) ብቻ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በት/ቤቱ ግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 7 መውሰድ ይችላሉ።
- ጨረታው ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆይና በ11ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ታሽጎ 4፡30 ሰዓት ላይ ይከፈታል። ተጫራቾች ከላይ በሰንጠረዡ /ሎት/ ማስከበሪያ ለእያንዳንዱ የተገለፁትን የገንዘብ መጠን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተረጋገጠ (CPO) ማቅረብ አለባቸው።
|
ሎት |
የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር (CPO) |
|
ሎት 1 |
5,000.00 (አምስት ሺህ ብር) |
|
ሎት 2 |
5,000.00 (አምስት ሺህ ብር) |
|
ሎት 3 |
15,000.00 (አስራ አምስት ሺህ ብር) |
|
ሎት 4 |
10,000.00 (አስር ሺህ ብር) |
|
ሎት 5 |
15,000.00 (አስራ አምስት ሺህ ብር) |
|
ሎት 6 |
10,000.00 (አስር ሺህ ብር) |
- ተጫራቾች ለሚያቀርቧቸው የዕቃ ናሙና ላይ የድርጅቱን ማህተም ሳይደረግ እዲቀርብ፣
- ተጫራቾች በሰነዱ ላይና ፓስታዎች ላይ የማጭበርበር ድርጊት ላለመፈፀም ፊርማና ማህተም በማድረግ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የጨረታ ሰነድ በሰንጠረዡ በተጠቀሰው የጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰዓት የእቃውን ዋጋ ቫትን ጨምሮ በመግለፅ በቢሮ ቁጥር 7 ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው ከላይ በተገለፀው የመክፈቻ ቀንና ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በት/ቤቱ ግዥ ክፍል ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ ፡- ኮ/ቀ/ክ/ከተማ አቡነ ባስልዮስ የቅ/የመ/ጀ/ደ/ት/ቤት ወይም በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- 011-8-34-22-19 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ የአቡነ ባስልዮስ ቅድመ አንደኛ እና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት
