በአብክመ የከሚሴ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በ2017 በጀት አመት የእግረኛ መንገድ (Walk Way) ለማሰራት በጠቅላላ ስራ ተቋራጭ የንግድ ፈቃድ ያላቸውን ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
የእግረኛ መንገድ (Walk Way) ስራ ብሄራዊ
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በአብክመ የከሚሴ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በ2017 በጀት አመት የእግረኛ መንገድ (Walk Way) ለማሰራት በጠቅላላ ስራ ተቋራጭ የንግድ ፈቃድ ያላቸውን ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በሥራው ለመሳተፍ ፈቃደኛ የሆኑ፡-
- በጠቅላላ ስራ ተቋራጭ ደረጃቸው GC/7 እና ከዚያ በላይ የሆኑ፤
- ስራው በጠቅላላ ስራ ተቋራጭ አግባብነት ያለው ህጋዊ ፈቃድ ኖሯቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉና ያሳደሱ፤ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ያላቸው፤ የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና TIN ያላቸው፡፡
- የጨረታውን ሰነድ ከከሚሴ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረት ልማት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 33 በግዢ/ፋይ/ ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ በ21 (ሃያ አንድ) ተከታታይ ቀናት ከላይ የተዘረዘሩትን መረጃዎች ዋናና ኮፒ በመያዝ ዘወትር በስራ ቀንና ሰዓት የማይመለስ የኢትዮጵያ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን የፋይናንሽያል ሰነድ ዋና እና ኮፒ በማድረግ ለየብቻው በታሸገ ኤንቨሎፕ በአብክመ ከሚሴ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሃያ ሁለተኛው ቀን (22ኛ ቀን) 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው በ17/5/2017 ዓ.ም በ22ኛው 4፡30 ሰዓት በግዢ /ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ቢሮ ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ 22ኛው ቀን ቅዳሜ እና እሁድ እንዲሁም የበዓል ቀን ከሆነ ቀጣይ ባለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ተመላሽ የሚደረግ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 225,000 (ሁለት መቶ ሃያ አምስት ሺህ ብር) በጥሬ ገንዘብ ወይንም በተረጋገጠ በባንክ ትዕዛዝ /CPO/ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- የጨረታ አሸናፊ የሆነው ድርጅት ውል በሚዋዋልበት ጊዜ የውለታ ማስከበሪያ ከአጠቃላይ ድምር ዋጋ 10% ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
- መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለፋይናንስ ግምገማ ያለፉት ተጫራቾች በቁጥር ቢያንስ 3 እና በላይ ከሆኑ በጨረታ አከፋፈት ወቅት ከተነበበው አጠቃላይ ዋጋ ላይ የሂሳብ ስሌት (አርቲሜቲክ ቼክ) ከተሰራ በኋላ የተደረሰበት ልዩነት እስከ 2.5% ድረስ ከሆነ ተቀባይነት የሚኖረው ሲሆን ከዚህ የበለጠ ልዩነት ካጋጠመ ከውድድር ውጭ ይሆናል፡፡
- ከ3 በታች ከሆኑ በጨረታ አከፋፈት ወቅት ከተነበበው አጠቃላይ ዋጋ ላይ የሂሳብ ስሌት (አርቲሜቲክ ቺክ) ከተሰራ በኋላ የተደረሰበት ልዩነት እስከ 1% ድረስ ብቻ ተቀባይነት የሚኖረው ሲሆን ከዚህ በላይ ከሆነ ከውድድር ውጭ ይሆናል፡፡
- የሂሳብ ስሌት (አርቲሜቲክ ቼክ) በግዥ ፈፃሚው መ/ቤት ባለሙያ ከሚስተካከለው ውጭ በተጫራቾች የሚቀርበው የመጫረቻ ሰነድ ላይ በነጠላ እና ጠቅላላ ዋጋ ላይ ስርዝ ድልዝ ካለ ተጫራቹ ከጨረታ ውጭ ይሆናል፡፡
- ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በከሚሴ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በግንባር በመቅረብ ወይንም በስልክ ቁጥር 033 554 02-55 ደውለው መረዳት ይችላሉ፡፡
በአብክመ የከሚሴ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት
