የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በ2017 በጀት ዓመት ለኮምፒውተሮች፣ ለሰርቨሮች እና ተዛማጅ ለሆኑ ዕቃዎች አገልግሎት የሚውል አንቲቫይረስ አቅራቢ ድርጅቶችን በግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ ከአሸናፊ ድርጅት መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መለያ ቁጥር ኢሎአ/004/2017
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በ2017 በጀት ዓመት ለኮምፒውተሮች፣ ለሰርቨሮች እና ተዛማጅ ለሆኑ ዕቃዎች አገልግሎት የሚውል አንቲቫይረስ አቅራቢ ድርጅቶችን በግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ ከአሸናፊ ድርጅት መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅቶች ሁሉ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ እስከ የካቲት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ድረስ ለዚህ ሥራ የተዘጋጀውን የጨረታ ሠነድ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈልና በመግዛት መወዳደር ይችላሉ፤
ተጫረቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000 (ሃምሳ ሺህ ብር) በሲፒኦ፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ወይም በጥሬ ገንዘብ ገቢ አድርገው ዋናውን ማስረጃ ማያያዝ አለባቸው። ተጫራቾች በስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ውስጥ የተደራጁ ህጋዊ ጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት በጨረታው ለመወዳደር የጨረታ ማስከበሪያ ማስያዝ ያለባቸው ከአደራጃቸው ተቋም የሚያቀርቡት የድጋፍ ደብዳቤ ውስጥ መካተት ያለባቸው ሁኔታዎች የሚወዳደሩበትን ተቋም ስም፣ የሚወዳደሩበትን የግዥ ዓይነት፣ የጨረታ ቁጥር እና የጨረታ ማስከበሪያውን የገንዘብ መጠን በግልጽ በአሃዝና በፊደል የተፃፈ የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ አለባቸው።
ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶችን የቴክኒካልና ፋይናንሻል ሰነዶችን የያዘ አንድ ዋና እና አንድ ቅጂ ለየብቻው በፖስታ በማድረግና በፅሁፍ በመለየት የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ የምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር የምስክር ወረቀት፣ በጨረታ ለመሳተፍ የሚያገለግል ክሊራንስ፣ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡበትን የምስክር ወረቀት፣ የማጭበርበር ድርጊት ላለመፈፀም ቃል የሚገባበት ቅፅ ሞልታችሁ ማህተምና ፊርማ አድርጋችሁ የመጫረቻ ሰነዶቻችሁን አሟልታችሁ በማቅረብና የጨረታ ማስከበሪያውን በታሸገ ፖስታ በማድረግ እስከ የካቲት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ በዚሁ ሥራ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ገቢ ማድረግ አለባቸው፡፡
ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት የካቲት 25 ቀን 2017 ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት ፒያሳ ጣይቱ ሆቴል አጠገብ በሚገኘው የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ዋና መ/ቤት ይከፈታል፡፡ አገልግሎቱ ስለጨረታው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-126-78-16 ደውሎ መረዳት ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት
