አዲስ የተቀናጀ የልማት ድርጅት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በተለያዩ ወረዳዎች በትምህርት፣ በጤና እና በወጣት ልማት ዘርፎች በርካታ የልማት ሥራዎችን በማከናወን ላይ የሚገኝ በጎ አድራጎት ድርጅት ነው፡፡ ድጋፍ ለሚያደርግላቸው ተማሪዎች የጆሮ ማዳመጫ መሣሪያ እና ድጋፍ ለሚያደርግላቸው ወላጆች የዶሮ ጫጩት 70 ቀን እድሜ ያላቸው/ ብዛት 1250 የዶሮ ጫጩት መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
አዲስ የተቀናጀ የልማት ድርጅት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በተለያዩ ወረዳዎች በትምህርት፣ በጤና እና በወጣት ልማት ዘርፎች በርካታ የልማት ሥራዎችን በማከናወን ላይ የሚገኝ በጎ አድራጎት ድርጅት ነው፡፡
ድርጅታችን:-
- ድጋፍ ለሚያደርግላቸው ተማሪዎች:
- የጆሮ ማዳመጫ መሣሪያ /Hearing Aids/ (107) × TM × P P4 ብዛት 2
- የጆሮ ማዳመጫ መሣሪያ /Hearing Aids/ (106) × TM x P P4 ብዛት 4 መግዛት ይፈልጋል፡፡
- ድጋፍ ለሚያደርግላቸው ወላጆች የዶሮ ጫጩት 70 ቀን እድሜ ያላቸው/ ብዛት 1250 የዶሮ ጫጩት መግዛት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም ፤
- በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው እና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው፣
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 2% ቢድ ቦንድ በባንክ የክፍያ ትዕዛዝ CPO ወይም ተመጣጣኝ ሰነድ ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፣
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ወይም /Tin Number/ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ያላቸው ወይም ከተጨማሪ እሴት ታክስ ክፍያ ነፃ ስለመሆናቸው የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ያላቸው ተጫራቾች፣ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 07 /ሰባት/ የሥራ ቀናት ውስጥ ክፍለ-ሃገር አውቶቡስ ተራ አዲሱ ሚካኤል አካባቢ በሚገኘው የድርጅቱ ጽ/ቤት በመቅረብ የምትሸጡበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ለጨረታ ማስገቢያ በተዘጋጀ ሣጥን ውስጥ አስገብታችሁ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን ድርጅቱ ይጋብዛል፡፡
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት በ8ኛው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 3:00 ላይ ተዘግቶ ከጠዋቱ 4:00 ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል። ስምንተኛው ቀን ቅዳሜ ወይም እሁድ ላይ ከዋለ የሚቀጥለው ሰኞ ጨረታው የሚከፈትበት ዕለት ይሆናል፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ :-
ስልክ 011-276-35-39/011-213-18-29/09 96 23 09 27
አዲስ የተቀናጀ የልማት ድርጅት
