Tender Detail

Tender Details

  • Company BRANNA PRINTING ENTERPRISE (ብራና ማተሚያ ድርጅት)
  • Address ከወሎ ሰፈር ወደ ጎተራ በሚወስደው መንገድ 700 ሜትር ላይ በስተግራ በኩል : አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0114 42 64 80
  • Website
  • Deadline04 Jun 2025, 12:00 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date2025-06-04 00:00:00
  • Categories Machinery

የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ ብራና ማተሚያ ድርጅት ተገቢ ዕድሳት የተደረገላቸው (Refurbished) ና በጥሩ ይዞታ ላይ ያሉ ማሽኖች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡


 

ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

ቁጥር 010/2017

 

ልፅ ጨረታ ማስታወቂያ ብራና ማተሚያ ድርጅት ተገቢ ዕድሳት የተደረገላቸው (Refurbished) በጥሩ ይዞታ ላይ ያሉ ማሽኖች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህም መሠረት በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተገለፁትን መስፈርቶች በማሟላት መሳተፍ ትችላላችሁ።

1 በዘርፉ በዘመኑ የታደሰ የንግድ ምዝገባ ማቅረብ የሚችሉ፣

2 የዘመኑን ግብር የከፈሉና ለዚህም ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣

3 የግብር ከፋይነት መለያ ሠርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ፣

4 የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና ሠርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ፣

5 ግብር የመፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ ከግብር ሰብሳቢው ባለሥልጣን ጨረታ ላይ መሳተፍ እንዲችሉ የተሰጠ ሊራንስ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣

6 በመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ በአቅራቢነት ለመመዝገባቸው ማስረጃ ያላቸው፤

7 ተጫራቾች ለጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር አምስት መቶ (500.00) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት (ቅዳሜ ግማሽ ቀንን ጨምሮ) ወሎ ሰፈር በሚገኘው ዋና መሥሪያ ቤት ቢሮ ቁጥር 32 በአካል በመምጣት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ።

8 ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ያቀረቡትን ዋጋ 2% በሲፒኦ (CPO) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፣

9 ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ የማስረከቢያ ጊዜ መጥቀስ አለባቸው፣

10 ተጫራቾች በጨረታው ያሸነፏቸውን ማሽኖች ድርጅቱ መጋዘን ድረስ ማድረስ አለባቸው፣

11 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት 11ኛው የሥራ ቀን እስከ 800 (ከሰዓት) ድረስ በሰም በታሸገ ፖስታ ለጨረታ ማስገቢያ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በእለቱ ከቀኑ 800 ሰዓት ታሽጎ ከቀኑ 830 በድርጅቱ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡

12 ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው

 

አድራሻ፡- ከወሎ ሰፈር ወደ ጎተራ በሚወስደው መንገድ 700 ሜትር ላይ በስተግራ በኩል

ስልክ ቁጥር፡- 0114 42 64 80

 

ብራና ማተሚያ ድርጅት

 

Save Tender