የባሌ ዞን ማረሚያ ቤት በማረሚያ ቤቱ ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች አገልግሎት የሚውሉ ከሀምሌ 01 ቀን 2017 ዓ/ም እስከ ታህሳስ 30 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ የሚቀርብ የምግብ እህሎች ማጣፈጫ ቅመማ ቅመሞች እና ድፍን የማገዶ እንጨት በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ባ/ዞ/ማ 05/2017
የባሌ ዞን ማረሚያ ቤት በማረሚያ ቤቱ ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች አገልግሎት የሚውሉ ከሀምሌ 01 ቀን 2017 ዓ/ም እስከ ታህሳስ 30 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ የሚቀርብ የምግብ እህሎች ማጣፈጫ ቅመማ ቅመሞች እና ድፍን የማገዶ እንጨት በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን የጨረታ መስፈርቶችን የሚያሟሉ የንግድ ድርጅቶች በጨረታው መወዳደር ይችላሉ።
- ተጫራቾች በሚወዳደሩበት ዘርፍ የ2017 ዓ.ም የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳቸውን (Trade license) የንግድ ምዝገባ ወረቀት: የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) የቲኦቲ (TOT) የግብር ከፋይ መለያ (TIN) ሰርተፍኬት ምዝገባ ማስረጃ: የአቅራቢነት ምዝገባ ማስረጃ (Supplier list) ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት የስራ ቀን ጀምሮ ለ5 ተከታታይ የሥራ ቀናት የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 100 (አንድ መቶ) ብር በመክፈል ከባሌ ዞን ማረሚያ ቤት ከቢሮ ቁጥር 5 መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 15,000.00 (አስራ አምስት ሺህ ብር) የያዘ ሲፒኦ ብቻ ህጋዊ እውቅና ካለው ባንክ በማቅረብ መወዳደር አለባቸው።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ እና የቴክኒካል ኦሪጂናል ሰነድ ለ2017 ዓ.ም የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳቸውን (Trade license) የንግድ ምዝገባ ወረቀት: የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) የግብር ከፋይ መለያ (TIN) ሰርተፍኬት የአቅራቢነት ምዝገባ ማስረጃ (Supplier list) ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት የስራ ቀን ጀምሮ የሚጫረቱባቸውን ሰነዶች በመግዛት ኦሪጂናል ፋይናንሺያል (ዋጋ የተሞላበት) ሰነድ ፋይናንሺያል ኮፒ ሰነድ እንዲሁም ቴክኒካል ኦሪጂናል ሰነድ ሶስቱንም ሰነዶች በተለያዩ ፖስታዎች አሽገው ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት የጨረታው ሳጥን እስከሚታሸግበት እለት እና ሰዓት ድረስ ማስገባት ይችላሉ።
- እያንዳንዱ ሰነድ እና የታሸገ ፖስታ ላይ የድርጅቱ ኃላፊ ፊርማ እና ማህተም መኖር አለበት።
- ጨረታው በጋዜጣ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ዕለቱ በዓል ወይም ዝግ ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን ጨረታው ይከፈታል።
- በጥቃቅን እና አነስተኛ ንግድ ተደራጅተው የበሰለ ምግብ ለማቅረብ የሚቀርቡ ማህበራት ቅድሚያ ይሰጣቸዋል።
- ተጫራቾች ማሸነፋቸው በደብዳቤ ከተገለፀላቸው ከ5 ቀን በኋላ ከ6ኛው ቀን ጀምሮ በ15 የስራ ቀናት ውስጥ መ/ቤቱ ቀርበው ውል መፈራረም አለባቸው። ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ
በስልክ ቁጥር፡- 022 244 00023/09 32 31 12 24 ደውለው ይጠይቁ።
የባሌ ዞን ማረሚያ ቤት
