የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት የተለያዩ ጣውላና እንጨት ምርቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ከ6 ወር እስከ 1 ዓመት ውል ፈጽሞ የተጠቀሰውን የግንባታ ግብዓት ማቅረብ ከሚችሉ ድርጅቶች መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የተለያዩ ጣውላና እንጨት ምርቶች ግዥ ጨረታ ቁጥር 36/2017
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት የተለያዩ ጣውላና እንጨት ምርቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ከ6 ወር እስከ 1 ዓመት ውል ፈጽሞ የተጠቀሰውን የግንባታ ግብዓት ማቅረብ ከሚችሉ ድርጅቶች መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም
- በጨረታው ለመካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችል በዘርፉ የተሰጠ የታደሠ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉ ፤ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ፤ ክሊራንስ እና የአቅራቢነት ምዝገባ ውስጥ የተመዘገቡ ለመሆናቸው ማስረጃ ኮፒ አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ፤ ድርጅቶችና ግለሰቦች የጨረታ ሠነድ የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ) ብር በመክፈል በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቃሊቲ ማሰልጠኛ ፊት ለፊት የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን እና CCRDA መካከል ወደ ውስጥ ገባ ብሎ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት ቢሮ በመቅረብ የተዘጋጀውን የጨረታ ሠነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 30,000 (ሰላሳ ሺህ ብር) በባንክ የተረጋገጠ ቼክ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የ90 ቀናት የባንክ ጋራንቲና (unconditional bid bond guarantee) ከሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ቴክኒካል ሰነድ ጋር በማያያዝ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት በአየር ላይ የሚቆይ ሆኖ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 በድርጅቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተሳታፊዎች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ግንባታና ማማከር ድርጅት የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡- በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቃሊቲ ማሰልጠኛ ፊት ለፊት
የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ቢሮ አጠገብ ስልክ ቁጥር 011 462 1457 /09 11 094 817
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት
