በኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የምርጥ ዘር አቅርቦት ዘርፍ በአሰላ፣ አርዳይታ፣ ኮፈሌ ፣ ሀዋሳ፤ ነቀምት፣ ቦንጋ፣ እና ባህርዳር ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች የሚገኘውን የምግብ እህል እና የብጣሪ እህል በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
የምግብ እህል እና የብጣሪ እህል ለመሸጥ የወጣ
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ኢግስኮ-ምዘአዘ/ጨሸ/03ሠነድ/2017
በኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የምርጥ ዘር አቅርቦት ዘርፍ በአሰላ ፣ አርዳይታ ፣ ኮፈሌ ፣ ሀዋሳ ፣ ነቀምት ፣ ቦንጋ ፣ እና ባህርዳር ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች የሚገኘውን የምግብ እህል እና የብጣሪ እህል በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ስለሚፈልግ፡-
- ማንኛውም ተጫራች በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላችሁ እና የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈሉ፣
- ማንኛውም ተጫራች ለጨረታው ዋስትና ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን ከ2% ያላነሰ CPO በኢትዮጵያ ምርጥ ዘርና የደን ውጤቶች አቅርቦት ዘርፍ ስም ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የጨረታውን ሰነድ ዘወትር በሥራ ሰዓት (ከ11፡00 ሰዓት በፊት) በዋናው መ/ቤት የግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅርቦት ዘርፍ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 04 የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የተገለፀውን መጠን የምግብ እህል እና የብጣሪ እህል መጫረት ይችላል፤
- ማንኛውም ተጫራች የምግብ እህሉ እና የብጣሪ እህሉ በሚገኙበት ቅ/ጽ/ቤቶች በመገኘት አይቶ መጫረት አለበት፡፡ ይህን ሳያደርግ ዋጋ ቢያቀርብ ኃላፊነቱ የተጫራቹ ይሆናል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ የሚጠይቀውን በሙሉ አሟልቶ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች በሌላ ተጫራች ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይችልም ።
- የምግብ እህል እና የብጣሪ እህል መጠን በዚህ ጨረታ ሠነድ ላይ ከተገለፀው መጠን ሊያንስ ይችላል።
- ዋጋውን በኤንቨሎፕ በማሸግ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ማስገባት የሚቻል ሲሆን ጨረታው ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዘርፍ ጽ/ቤት አዳራሽ እና ከላይ በተጠቀሱት ቅ/ጽ/ቤቶች ጨረታው ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ስልክ ቁጥር 011 6 18 61 25
የኢትዮጵያ ምርጥ ዘርና የደን ውጤቶች አቅርቦት ዘርፍ
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
