የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት በሀዋሳ እና በሆሳዕና በድርጅቱ መጋዘኖች ተከማችቶ የሚገኝ ከዘርነት የተረፈ ለምግብነት የሚውል ንፁህ የቦቆሎ እና ንጹህ የስንዴ እህል በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ C0012/ሽያጭ/18ዓ.ም
የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት በሀዋሳ እና በሆሳዕና በድርጅቱ መጋዘኖች ተከማችቶ የሚገኝ ከዘርነት የተረፈ ለምግብነት የሚውል ንፁህ የቦቆሎ እና ንጹህ የስንዴ እህል በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሰረት፡-
- ተጫራቾች በሥራ ዘርፉና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎች የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ፣ የግብርከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታው ውድድር ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ በየሎት 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ/ ሲሆን የሎት ብዛት እና የእህሉ መጠን በሚሸጥ ሰነድ ላይ የሚገለጽ ይሆናል፡፡ የጨረታ ማስረከቢያ በባንክ የተመሰከረለት የከፍያ ማዘዣ (CPO) ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የጨረታው ሰነድ ይህ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው ቀን ድረስ የማይመለስ ብር 400 በመከፈል በሀዋሳ ከተማ በድርጅቱ የግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ከፍል ቢሮ ቁጥር12 መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 ቀናት ውስጥ በሰም በታሸገ ፖስታ/ኤንቨሎፕ/ በማድረግ አሪጂናልና ኮፒውን ለየብቻው ከተጓዳኝ ማስረጃዎች ጋር በማደራጀት በድርጅቱ የስብሰባ አደራሽ ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ በ10ኛው ቀን እስከ 8፡00 ሰዓት ማስገባት አለባቸው፡፡
- የጨረታው ሳጥን የጨረታው ማስታወቂያ በወጣ 10ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ታሽጐ በእለቱ በ8፡3ዐ ሰዓት በድርጅቱ የስብሰባ አደራሽ ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው/ በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ነገር ግን 10ኛው ቀን የሥራ ቀን ባይሆን በቀጣዩ የሥራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ተመሳሳይ ቦታ ሰዓትና ሁኔታ ይከፈታል፡፡
- ድርጅቱ ለዚሁ ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
በስልክ ቁጥር 046 220 1752/2285/2117
የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት ሀዋሳ
✨ messages.ai_summary
South Best Seed Enterprise offers for sale by tender clean food-grade faba beans and wheat grain stored at its Hawassa and Hosaena warehouses. Bidders must hold a renewed trade license and TIN.
