ኮርፖሬሽናችን ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ላሉት የተለያዩ ኤክስካቫተሮች አገልግሎት የሚሆኑ ጃክሀመሮች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በድጋሜ የወጣ የግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር ዘመን/ማሽግ 13/2017
ኮርፖሬሽናችን ላሉት የተለያዩ ኤክስካቫተሮች አገልግሎት የሚሆኑ ጃክሀመሮች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን፤
- በዘርፉ ለዘመኑ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድና፤ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) እና የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ያለው/ያላት
- የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን ቫትን ጨምሮ 2% በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ (CPO) ወይም /unconditional bank gurantee/ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርበታል።
- የጨረታ ሰነዱን ባ/ዳር ከተማ ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ቀበሌ 11 እና አ/አበባ ለገሀር አመልድ ኢትዮጵያ ህንጻ 7ኛ ፎቅ በሚገኘው ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ቢሮ የጨረታ ሰነዱ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት መውሰድ ይችላሉ።
- የጨረታ መዝጊያ እና መክፈቻ ቀናት ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ሰነዶች ኦርጅናልና ኮፒውን በመለየት በተለያዩ ፖስታዎች በጥንቃቄ በማሸግ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን (15 ተከታታይ ቀናት በመቁጠር) ድረስ ብቻ በኮርፖሬሽናችን የማሽ/ተሽ/መ/ግዥና አቅ/ኬዝ ቲም ቢሮ (ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበብ ህንጻ አካባቢ የቀድሞው የአማራ ከተሞች ልማት አ.ማ ግቢ ውስጥ) በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው በ15ኛው ቀን በተራ ቁጥር 4 በተገለጸው ቦታ በ8፡00 ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ 8፡30 ይከፈታል። የመዝጊያና መክፈቻ ቀኑ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን እስከ ቀኑ 8፡00 ሠዓት ድረስ ማስገባት የሚችሉ ሲሆን በዚያኑ ቀን 8፡00 ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ 8፡30 ይከፈታል።
- ዝርዝር የጨረታ መመሪያውን እና የውል ይዘቱን እንዲሁም የሚገዙትን እቃዎችና አገልግሎቶች፤ ዝርዝር ቴክኒካል መገምገሚያዎች በሙሉ ከጨረታ ሰነዱ ውስጥ የተገለፀ ስለሆነ ማንኛውም ተጫራች በጥንቃቄ በማንበብ ዋጋቸውን በጨረታ መመሪያው መሰረት መሙላት አለበት።
ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ስልክ ቁጥር፡- 058-3205185/0918164393/0918784490
ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን
