የወልቂጤ ማረሚያ ተቋም ለህግ ታራሚዎች ለቀለብ አገልግሎት የሚውል ከዚህ በታች በሠንጠረዡ ውስጥ የተመለከቱትን አቅርቦቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለ3 ወራት በሚቆይ የአቅርቦት ጊዜ ሆኖ በአቅራቢና ተቀባይ መካከል በሚደረገው የውል ስምምነት መሠረት ሶስት ወራት ለሚደርስ የግዥ ዘዴ በየወሩ ለሚያቀርቡ አቅራቢዎች አወዳድሮ ለመስጠት ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡- ወማተ/11/1779/28/09/17
የወልቂጤ ማረሚያ ተቋም ለህግ ታራሚዎች ለቀለብ አገልግሎት የሚውል ከዚህ በታች በሠንጠረዡ ውስጥ የተመለከቱትን አቅርቦቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለ3 ወራት በሚቆይ የአቅርቦት ጊዜ ሆኖ በአቅራቢና ተቀባይ መካከል በሚደረገው የውል ስምምነት መሠረት ሶስት ወራት ለሚደርስ የግዥ ዘዴ በየወሩ ለሚያቀርቡ አቅራቢዎች አወዳድሮ ለመስጠት ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የአቅርቦቱ አይነት |
መለኪያ |
የአቅርቦት መጠን |
የማቅረቢያ ጊዜ |
ርክክቡ የሚፈፀምበት ቦታ |
በቅድሚያ ለ03 ወራት ቆይታ ጊዜ ከ-እስከ |
|
1 |
ነጭ ሠርገኛ ጤፍ |
በኩ/ል |
ከ80-150 ኩንታል |
ወር በገባ ከ25-30 ድረስ |
ተቋሙ ቅጥር ግቢ |
ከ1/11/2017-30/01/2018 |
|
2 |
ነጭ ቦቆሎ |
በኩ/ል |
ከ100-150 ኩንታል |
ወር በገባ ከ25-30 ድረስ |
ተቋሙ ቅጥር ግቢ |
ከ1/11/2017-30/01/2018 |
|
3 |
ባቄላ |
በኩ/ል |
ከ30-50 ኩንታል |
ወር በገባ ከ25-30 ድረስ |
ተቋሙ ቅጥር ግቢ |
ከ1/11/2017-30/01/2018 |
|
4 |
ስነዴ |
በኩ/ል |
ከ15-25 ኩንታል |
ወር በገባ ከ25-30 ድረስ |
ተቋሙ ቅጥር ግቢ |
ከ1/11/2017-30/01/2018 |
|
5 |
የተፈጨ በርበሬ |
በኩ/ል |
ከ150-280 ኪ.ግራም |
ወር በገባ ከ25-30 ድረስ |
ተቋሙ ቅጥር ግቢ |
ከ1/11/2017-30/01/2018 |
|
6 |
የማገዶ እንጨት |
በሜ/ኩ |
ከ150-180 ሜ.ኩ |
ወር በገባ ከ25-30 ድረስ |
ተቋሙ ቅጥር ግቢ |
ከ1/11/2017-30/01/2018 |
|
7 |
ጎመን ዘር |
ኪ.ግ |
ከ20-50 ኪ.ግራም |
ወር በገባ ከ25-30 ድረስ |
ተቋሙ ቅጥር ግቢ |
ከ1/11/2017-30/01/2018 |
መመዘኛዎች ፡-
- በየመስኩ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፤ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያላቸው፤ ከማንኛውም ግብርና ታክስ ከፋይነት ነፃ እንዲሆኑ ከተፈቀደላቸው ድርጅቶችና ዩኒየኖችና ተመሳሳይ የንግድ ድርጅቶች በስተቀር የVAT 15% ተመዝጋቢ የሆኑና የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማስረጃ ሊያቀርቡ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች ለሚጫረቱበት አቅርቦት በቀደምት የሥራ ዘመን ተጫርተው በማሸነፍ ለማረሚያ ተቋማት ወይም መንግስታዊና ሕዝባዊ ድርጅቶች ለ01 (አንድ) አመት እና ከዚያም በላይ ለሆነ ጊዜያት ያለእንከን ስለማቅረባቸው የመልካም ሥራ አፈፃፀም ደብዳቤ /ምስክር ወረቀት/ ማስረጃ ከሌሎች መጫረቻ ሰነዶች ጋር አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ፤
- አሸናፊው ተጫራች ለአቅርቦቱ ከላይ በተዘረዘሩት መስፈርቶች መሠረት ሀምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ3 ወራቶች በየወሩ ለማቅረብ ህጋዊ የውል ሰነድ የሚፈርሙና ያሸናፊው ነጠላ ዋጋ እንደተጠበቀ ሆኖ ለማቅረብ ፈቃደኛ የሚሆኑ፤
- ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ወልቂጤ ማረሚያ ተቋም ግዥና ፋይናንስ ንብ/አስ/ደ/ሥራ ሂደት ቢሮ በመቅረብ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በነፃ መውሰድ የሚችሉ ሲሆን፤ የጨረታ ማስከበሪያን በሚመለከት ከጠቅላላ አቅርቦት ዋጋ 2% የብር 50,000 /ሃምሳ ሺህ ብር ብቻ/ /CPO/ ተመሳሳይ/ ሰነድ በማሰራት ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 /አስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት የእያንዳንዱን እህል የአንዱን ኩንታል ነጠላ ዋጋ ከነማስረጃው ኮፒዎች ጋር በማድረግ በታሸገ ኤንቨሎፕ አዘጋጅተው ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የእህል ዓይነቶችን ናሙና የማቅረብ ግዴታ እንዳለባቸው መዘንጋት የለባቸውም።
- ጨረታው በ16ኛው ቀን በ5፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ ተጫራቾች /ህጋዊ/ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ16ኛው በ5፡30 ሰዓት በማረሚያ ተቋሙ ቅጥር ግቢ አዳራሽ /ቢሮ/ የሚከፈት መሆኑን ስንገልጽ ዕለቱ የበዓላት /የእረፍት/ ቀን ከሆነ በማግስቱ በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት መሆኑን እያሳሰብን መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 011-3-30-01-54 / 011-3-30-11-39 / 011-3-30-15-68 ደውለው መጠየቅ የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ወልቂጤ ማረሚያ ተቋም
