የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በ2017 በጀት ዓመት በዋናው መስሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኘው አስፋልት በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ አሁን ላይ የተጎዳና የተቆፋፈረ በመሆኑ በአዲስ መልክ የአስፋልት ስራውን ለማሰራት ደረጃቸው GC/BC-3 እና ከዚያ በላይ የሆኑ የመንገድ ስራ ተቋራጮችን በግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መለያ ቁጥር ኢሎአ/007/2017
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በ2017 በጀት ዓመት በዋናው መስሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኘው አስፋልት በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ አሁን ላይ የተጎዳና የተቆፋፈረ በመሆኑ በአዲስ መልክ የአስፋልት ስራውን ለማሰራት ደረጃቸው GC/BC-3 እና ከዚያ በላይ የሆኑ የመንገድ ስራ ተቋራጮችን በግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅቶች ሁሉ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ሰኔ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ለዚሁ ስራ የተዘጋጀውን የጨረታ ሠነድ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈልና በመግዛት መወዳደር ይችላሉ። ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ማሲያዝ ያለባቸው ብር 250,000.00 (ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) በሲ.ፒ.ኦ /C.P.O/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ /Irrevocable or Unconditional Bank Guarantee from Recognized Bank of Ethiopia/ ማሲያዝ አለባቸው።
ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ውስጥ የተገለፁትን የቴክኒካል ሰነዶችን የያዘ አንድ ዋናና አንድ ቅጂ ለየብቻው፣ የፋይናንሻል ሰነድ የያዘ አንድ ዋናና አንድ ቅጂ ለየብቻው እንዲሁም የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትናውን ለብቻው በፖስታ በማሸግ ሁሉንም በአንድ ትልቅ ፖስታ በማድረግ እስከ ሰኔ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ለዚሁ ስራ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ገቢ ማድረግ አለባቸው።
ጨረታው ሰኔ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት ሰኔ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት ፒያሳ ጣይቱ ሆቴል አጠገብ በሚገኘው የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ዋና መ/ቤት ይከፈታል፡፡ አገልግሎቱ ስለጨረታው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 011-126-78-16 ደውሎ መረዳት ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት
