የዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ውል ይዞ ለሚገነባው ለአዊ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ግንባታ አገልግሎት የሚውሉ Granite paint እና Mineral sand paint አቅርቦትና ቅብ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ በመፈፀም ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ ጨረታ ቁጥር 24/2017
የዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ውል ይዞ ለሚገነባው ለአዊ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ግንባታ አገልግሎት የሚውሉ Granite paint እና Mineral sand paint አቅርቦትና ቅብ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ በመፈፀም ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን፤
- በዘርፉ ለዘመኑ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድና ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) እና የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት እና የንግድ ፈቃድ ለማደስ ግብር ስለመክፈላቸው የሚሰጥ ማስረጃ ያለው/ያላት፣ ጨረታ ለመካፈል የሚያስችል ሰርተፍኬት ማቅርብ የሚችሉ፤
- የጨረታ ማስከበሪያ ቫትን ጨምሮ የጠቅላላ ዋጋውን 2% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ወይም /unconditional bank guarantee/ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
- የጨረታ ሰነዱ ባ/ዳር ከተማ ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ቀበሌ 11 እና አ/አበባ ለገሀር አመልድ ህንፃ 7ኛ ፎቅ በሚገኘው ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 02 የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ/ በመክፈል ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት መውሰድ ይችላሉ፤
- የጨረታ መዝጊያ እና መክፈቻ ቀናት ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናልና ኮፒውን በመለየት በተለያዩ ፖስታዎች በጥንቃቄ በማሸግ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ባ/ዳር ዋናው መ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ በእለቱ 8፡00 ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ 8፡30 ይከፈታል፡፡ 15ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን እስከ ቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል ጨረታው የሚከፈተው ባህር ዳር ዋናው ቢሮ አንደኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 108 የግን/ግብ/ግዥ እና አቅርቦት ኬዝ ቲም ቢሮ ክፍል ነው፡፡
- ውድድሩ በእያንዳንዱ ሎት /በጥቅል/ ዋጋ የሚታይ ይሆናል፤
- ተወዳዳሪዎች ለውድድር ሲቀርቡ በሚወዳደሩበት ሎት የአቅርቦት እና ቅብ ሥራ ከዚህ በፊት ለመስራታቸው ህጋዊ ከሆነ ተቋም የመልካም ስራ አፈጻጸም ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
- ዝርዝር የጨረታ መመሪያው እና የውል ይዘቱ በጨረታ ሰነዱ ውስጥ የተገለፀ ስለሆነ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ በማንበብ ዋጋቸውን በጨረታ መመሪያው መሰረት መሙላት አለባቸው፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
ለማንኛውም ተጨማሪ ማብራሪያ ስልክ ቁጥር ባህርዳር 0582180538/0918021411/
09-13-27-60-57
አዲስ አበባ- 011-126-5652/-126-5145/0918705036
ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን
