ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዴቨሎፕመንት /ECD/ ከችግኝነት ያለፉ ቁጥራቸው 1000 የሚሆኑ የተለያዩ የዛፍ እና የፍራፍሬ አይነቶችን በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ከችግኝነት ያለፉ ፍራፍሬ እና ዛፎች ግዢ (Matured tree & Fruits) የጨረታ ማስታወቂያ
ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዴቨሎፕመንት /ECD/ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስድስት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ ፔስታሎዚ የህናፃት መርጃ ድርጅት /PCF/ ከተባለ አለም አቀፍ አጋር ድርጅት ጋር በመሆን "Mobile Toolkit for Climate Resiliance" የሚል ትኩረቱን በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ያደረገ ፕሮጀክት በመተግበር ላይ ይገኛሉ። በመሆኑም በነዚህ አጋር ትምህርት ቤቶች ላይ ከችግኝነት ያለፉ ቁጥራቸው 1000 የሚሆኑ የተለያዩ የዛፍ እና የፍራፍሬ አይነቶችን ለመትከል አቅደዋል። በመሆኑም ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች በውድድሩ ላይ እንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል።
- በዘርፉ የተሰማሩ መሆኑን የሚገልጽ ለዘመኑ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ፣
- ቲን ነምበር ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ፣
- የቫት /ቲኦቲ ተመዝጋቢ የሆኑ፣ እንዲሁም
- ችግኞቹን በተቀመጠው ስፔሲፊኬሽን መሠረት ማቅረብ የሚችሉ፣ የችግኞቹን ሳምፕል አቅርበው ማሳየት የሚችሉ፣
- ያሸነፉበትን ችግኝ በራሳቸው ትራንስፖርት አጓጉዘው ድርጅቱ ወደ ሚያዘጋጀው ስቶር/ማስቀመጫ ሥፍራ ማድረስ የሚችሉ፣
ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከታወጀበት እለት አንስቶ ለ5 (አምስት) ተከታታይ የሥራ ቀናት ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዴቨሎፕመንት /ECD/ ቢሮ በመምጣት የጨረታውን ሰነድ በነጻ በመውሰድ ችግኞቹን የምታቀርቡበትን ዋጋ በመሙላት በታሸገ ኤንቨሎፕ ገቢ አድርጋችሁ እንድትወዳደሩ እንገልፃለን፡፡
አድራሻ፡- ቦሌ አለም ህንፃ 7ኛ ፎቅ
ስልክ ቁጥር፡- 0982 88 28 26
አዲስ አበባ
ማሳሰቢያ፡- ድርጅታችን ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዴቨሎፕመንት /ECD/
