የምዕራብ ወለጋ ዞን ማረሚያ ቤት በ2018 ዓ/ም ለታራሚዎች ምግብ ዝግጅት የሚውሉ ጥሬ ሰብሎችና የተለያዩ ማጣፈጫዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የምዕራብ ወለጋ ዞን ማረሚያ ቤት በ2018 ዓ/ም ለታራሚዎች ምግብ ዝግጅት የሚውሉ ጥሬ ሰብሎችና የተለያዩ ማጣፈጫዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። ስለሆነም የሚከተሉትን የጨረታ መስፈርት የሚያሟሉ እና በተወዳዳሪዎች መመሪያ መሠረት ተጫራቾች ቀርበው እንዲወዳደሩ ተጋብዘዋል።
- ጥራት ያላቸውን የተጠየቁ ጥሬ ሰብሎች በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸው
- የተለያዩ ማጣፈጫዎችን እና የዳቦ ዱቄት ማቅረብ የሚችሉና በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸው።
- ለምግብ ማብሰያ የሚሆን ግንድላ /ማገዶ/ እንጨት ማቅረብ የሚችል
- ተወዳዳሪዎች የተጠየቁትን ናሙና ሙሉ በሙሉ ማቅረብ አለባቸው
- የ2017 ዓ/ም ግብር አጠናቅቀው የከፈሉበትን ማስረጃ የሚያቀርቡና ለታክስ ከፋይነት (TIN) (TOT)
- ለጨረታ ማስከበሪያ (CPO) 30,000.00 ብር ከኦርጅናል ማስረጃቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ፣
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ አስራ አምስት የስራ ቀናት ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር (100) በመክፈል የግዥ ክፍል ከምዕራብ ወለጋ ዞን ማረሚያ ቤት መግዛት ይችላሉ!
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዱን በምዕራብ ወለጋ ዞን ማራሚያ ቤት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፤
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዓይነቶች እንደዚሁም የድርጅቱን ስም በሚያቀርቡት ፖስታ ላይ በኦሪጅናሉና በኮፒው ላይ በግልጽ በመጻፍ በድርጅቱ ማህተም እና ፊርማ አስደግፈው ማቅረብ አለባቸው፤
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን በተለያየ ኤንቬሎፕ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
- የጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአስራ ስድስተኛው የስራ ቀን ከቀኑ በ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ 4:30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል ሆኖም የተወዳዳሪዎች አለመገኘት የጨራታውን መከፈት አያግድም፤
- ተጫራቾች በጨረታው አሸናፊ ሲሆኑ ዕቃዎቹን በራሳቸው ማጓጓዣ እስከ ገዥው ጽ/ቤት ድረስ ማቅረብ አለባቸው
- ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0577 71 01 93 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የምዕራብ ወለጋ ዞን ማረሚያ ቤት
