የአመያ ማረሚያ ተቋም ከሀምሌ 5/11/2017 እስከ ታህሳስ 30/2018 ዓ.ም ድረስ ስድስት ወር የሚበቃ ለህግ ታራሚዎች ምግብ አገልግሎት ላይ የሚውሉ የተለያዩ ጥራጥሬ እህሎችና ሸቀጣሸቀጦችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የአመያ ማረሚያ ተቋም ከሀምሌ 5/11/2017 እስከ ታህሳስ 30/2018 ዓ.ም ድረስ ስድስት ወር የሚበቃ ለህግ ታራሚዎች ምግብ አገልግሎት ላይ የሚውሉ የተለያዩ ጥራጥሬ እህሎችና ሸቀጣሸቀጦችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
- ነጭ ሠርገኛ ጤፍ በኩንታል
- የተፈጨ የበቆሎ ዱቄት በኩንታል
- የማሽን የተቆላ አተር ክክ በኩንታል
- ባቄላ ክክ የታጠበ በኩንታል
- ፉሩኖ ዱቄት 1ኛ ደረጃ በኩንታል
- ጨው በኩንታል
- በርበሬ በኪሎ
- ጎመን ዘር በኪሎ
- አብሽ በኪሎ
- ቀይ ሽንኩርት በኪሎ
- ነጭ ሽንኩርት በኪሎ
- እርሾ በፓኬት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚሁ መሰረት ለመጫረት የምትፈልጉ፡-
- የዘመኑን ግብር የከፈሉበት የታደሰ ንግድ ፈቃድ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ TIN ነምበር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ወረቀትና በመንግስት ግዥ ላይ አቅራቢነት የተመዘገበ መሆኑን የሚገልጽ ፎቶ ኮፒ ማቅረብ የሚችል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ ብር 5,000 /አምስት ሺህ ብር/ በባንክ የተረጋገጠ CPO ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፣
- ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 10 ቀናት ውስጥ አመያ ማረሚያ ተቋም በመቅረብ የጨረታ ዶክመንትን በ100 ብር በመግዛት ዋጋ በመሙላት የድርጅታችሁን ማህተም በማድረግ የጨረታ ፖስታ በማሸግ በአመያ ማረሚያ ተቋም ለዚሁ ዓላማ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሣጥን የሚከፈተው በቀን 16/11/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ እለት በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአመያ ማረሚያ ተቋም ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
- ከ10000 ብር በላይ ግዥ 2% ዊዝ ሆልዲንግ ያስከፍላል፡፡
ለበለጠ መረጃ ፡- በአመያ ማረሚያ ተቋም ስልክ 0472270299/262 /538 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
በደ/ም/ኢት/ያ ሕ/ክ/መንግስት ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን
የአመያ ማረሚያ ተቋም
