በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የደብረብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል ከዚህ በታች የተመለከቱትን የተሸከርካሪ ኢንሹራስ አገልግሎት በብሄራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል ፡፡
ብሄራዊ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር-ግጨ01/2018
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የደብረብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል ከዚህ በታች የተመለከቱትን የተሸከርካሪ ኢንሹራስ አገልግሎት በብሄራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል ፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፣
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው፣
- የግዥው መጠን ብር 200000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር ከ1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የአገልግሎት ግዥ ፍላጎት ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች እያንዳንዱን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በማዕከሉ ገንዘብ ያዢ ቢሮ 05 ድረስ በመቅረብና በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት የተሸከርካሪ ኢንሹራንስ አገልግሎት ግዥ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ብር 20000.00 (ሃያ ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (CPO)ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ በደብረብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል ስም በመክፈል የተከፈለበትን ደረሰኝ ከሰነዱ ጋር አብረው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በጥንቃቄ አሽገው በደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል በግዥ ባለሙያዎች ቢሮ ቁጥር 03 ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ይህ ማስታወቂያ በግልጽ ጨረታ ከወጣበት ዕለት አንስቶ በመቁጠር በተከታታይ ቀናት እስከ 16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በደ/ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል የግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 03 በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት አንስቶ በሚቆጠር በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ እለት በ4፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡
- በጨረታው የሚሳተፉ ተጫራቾች የአገልግሎት ግዥው ተጫራቾች በደ/ብርሃን ከተማ የተሟላ አገልግሎት መስጠት የሚችል ቅርንጫፍ ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- የግዥ ፈፃሚ መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- በጨረታው መሳተፍ ለሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በደብረብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል የግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 03 ድረስ በአካል በመገኘት በስልክ ቁጥር 0116736918 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
የደብረብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል
ደ/ብርሃን
