በአብክመ በምስራቅ ጎጃም ዞን የባሶ ሊበን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ለባሶ ሊበን ወረዳ እንስሳት ሃብት ልማት ተጠሪ ጽ/ቤት የእንስሳት መድሃኒት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በአብክመ በምስራቅ ጎጃም ዞን የባሶ ሊበን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ለባሶ ሊበን ወረዳ እንስሳት ሃብት ልማት ተጠሪ ጽ/ቤት የእንስሳት መድሃኒት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ተጫራቾች
- ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና ፍቃዳቸውን ያሳደሱ፣
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN ያላቸውና ማቅረብ የሚችሉ፣
- ተጫራቾች ከላይ ከተራ ቁጥር 1-2 የተጠቀሱ ማስረጃዎችን ፎቶ ኮፒ በማድረግ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ 1% /አንድ ፐርሰንት/ በመሂ-1፤ በC.P.O ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸዋል::
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ግዥ ቢሮ ቁጥር 3 በመምጣት የማይመለስ 50 ብር ከፍለው መግዛት ይችላሉ።
- ይህ ግልፅ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ለ15 ቀን በአየር ላይ ውሎ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥን ታሽጎ በእዚሁ እለት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 3 በግልጽ ይከፈታል፡፡ ሆኖም የመክፈቻ ቀኑ በዓል ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀናት የሚከፈት ይሆናል፡፡
- በጨረታው አሸናፊ የሆነው ድርጅት አሸናፊነቱ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ከ 5 ተከታታይ የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የውል ማስከበሪያ 10% በማስያዝ ውል መፈጸም አለበት፡፡ በተገለጸው የጊዜ ገደብ ያልቀረበና ውል ያልፈጸመ እንደሆነ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙትን ገንዘብ መ/ቤቱ ውርስ ያደርጋል፡፡
- ውድድሩ በሎት ወይም በጥቅል ዋጋ የሚለይ በመሆኑ ተጫራቾች ሁሉንም መሙላት እና በዋጋ መሙያ ሰነዱ ላይ የድርጅቱን ማህተም፣ ስም እና ፊርማ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡
- አሸናፊው የአሸነፈበትን ኦርጅናል እና ትክክለኛ የተጠቀሱትን እቃዎች ጽ/ቤቱ ድረስ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች ዋጋ መሙያው ሰነዱ ላይ ምንም ዓይነት ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም ስርዝ ድልዝ ካለው ፓራፍ መደረግ አለበት፡፡
- መስሪያ ቤቱ በጨረታው የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
- የመንግስትን የግዥ መመሪያ አዋጅና ከላይ የተዘረዘሩትን ማዘዣዎች ካላሟላ ተጫራች ከውድድር ውጭ ይሆናል፡፡
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0582460316 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የአብክመ በምስራቅ ጎጃም ዞን የባሶ ሊበን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
