የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እ.ኤ.አ ከሴፕቴምበር 13-20/2025 በጃፓን ቶኪዮ ለሚካሄደው ውድድር ላይ የሚውሉ መጽሔት ለማሳተም በጨረታ ሰነዱ በተገለፀው ስፔስፊኬሽን መሠረት በሀገር ውስጥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሣተም ይፈልጋል::
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እ.ኤ.አ ከሴፕቴምበር 13-20/2025 በጃፓን ቶኪዮ ለሚካሄደው ውድድር ላይ የሚውሉ መጽሔት ለማሳተም በጨረታ ሰነዱ በተገለፀው ስፔስፊኬሽን መሠረት በሀገር ውስጥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሣተም ይፈልጋል::
በዚሁ መሰረት:-
1. በጨረታው ለመወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ የቲን እና ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፣
2. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ብር 5,000.00 (አምስት ሺህ ብር) ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው::ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን ቴክኒካልና ፋይናንሻል ለብቻው በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የሥራ ቀናት በፌዴሬሽኑ ቢሮ ቁጥር 5 ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል::
3. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ11ኛው ቀን የጨረታ ሳጥኑ ከረፋዱ 4፡00 ታሽጐ በዚያው ቀን 4፡30 ሰዓት በፌዴሬሽኑ ቢሮ ቁጥር 5 (መሰብሰቢያ አዳራሽ) ይከፈታል:: የመክፈቻ ቀን ቅዳሜ፣ እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፤
4. ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን የመጽሔት ዋጋ ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ እና ሳምፕል ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል!
5. ተጫራቾች የውስጥ ገጽ ዲዛይንና ህትመት መስራት ይጠበቅባቸዋል፤
6. ተጫራቾች ጨረታውን በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ) በመክፈል ጉርድ ሾላ በሚገኘው በፌዴሬሽኑ 2 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 5 በመምጣት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ!
7. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
አድራሻ፦ጉርድ ሾላ አትሌቲክስ ፌዲሪሽን ሕንጻ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6
ለበለጠ መረጃ፦ 09 17 01 25 04/ 09 83 31 00 39 ደውለው መጠየቅ ይችሳሉ::
ፋክስ 0116-45-879
ፓ.ስ.ቁ 13336
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክስ ፌደሬሽን
