• የእንስሳት መድሀኒት ግዥ ጨረታ
የጨረታ ማስታወቂያ
የቤ/ጉ/ክ/መ/ግብርና ቢሮ
- የእንስሳት መድሀኒት ግዥ ጨረታ ቁጥር 01/2018ዓ/ም–ሎት-01
- የእንስሳት ህክምና መገልገያ ቁሳቁሶችን ግዥ ጨረታ ቁጥር 02/2018ዓ/ም--ሎት-02
- የውሃ መሳቢያ ፓምፕ መለዋወጫ ዕቃዎች ግዥ ጨረታ ቁጥር 03/2018ዓ/ም--ሎት-03 ከላይ ከሎት -01-03 ያሉትን ግዥ ለመፈፀም የዘመኑን ግብር የከፈሉ፤ለ2017/18ዓ/ም በዘርፉ የታደሠ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ፤ ለ2017/18ዓ/ም የታደሰ የንግድ ምዝገባ ምስከርወረቀት፤በሀገር ውስጥ ገቢዎች የጨረታ ተሳታፊነት የድጋፍ ደብዳቤ ያለውን የታደሠ የአቅራቢነት ሰርተፊኬት ያላቸውን ተወዳዳሪዎች በሀገር ውስጥ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
1. ዝርዝር ጨረታውን የያዘ ሠነድ የማይመለስ ብር 500/አምስት መቶ ብር/በመከፈል አሶሳ በቤ/ጉ/ከ/መ/ግብርና ቢሮ በግዥ/ንብ/አስ/ዳይሬከቶሬት በመቅረብ መግዛት ይቻላሉ፡፡
2. የጨረታ ማስከበሪያ 2% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
3. አሸናፊ ድርጅት የውል ስምምነት ሲፈርም ለውል ማስከበሪያ ካሸነፈበት ጠቅላላ ዋጋ 10% ያስይዛል፡፡
4. በጨረታው ያልተመረጡ ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ የጨረታ አሸናፊ እንደታወቀ ወዲያውኑ ተመላሽ ይደረግላቸዋል፡፡
5. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት የጨረታ ሠነዱን በመግዛት እስከ 16ተኛው ቀን ከጥዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
6. ጨረታው የሚዘጋበት ቀን በ16ኛው የስራ ቀን ከጥዋቱ 4፡00 ሰዓት ሆኖ ነገር ግን ቅዳሜ እሁድ እና የህዝብ በዓል ቀን ላይ ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይዘጋል፡፡
7. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በ16ኛው የስራ ቀን ከጥዋቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አሶሳ በሚገኘው በቤ/ጉ/ከ/መ/ግብርና ቢሮ በግዥ ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት ይሆናል፡፡
8. ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ፡- 0577752144 አሶሳ ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ
