የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ የተለያዩ የእህል ዘር አጨዳና ምርት ማጓጓዝ አገልግሎት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር OSE/NCB/004/2018
የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ የተለያዩ የእህል ዘር አጨዳና ምርት ማጓጓዝ አገልግሎት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም አስፈላጊውን መስፈርት የምታሟሉ በጨረታው መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እየገላጽን ተጫራቶች፡-
- የንግድ ምዝገባ ሰርትፍኬት
- የዘመኑን የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርተፊኬት፣
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (Tin No)
- የአቅራቢነት ማስረጃ (Supplier List)
- የሚፈለግባቸውን የመንግሥት ግብር ስለመወጣታቸው የሚገልጽ ማስረጃ፣ ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር በማያያዝ ማቅረብ አለባቸው፡፡
ተጫራቾች ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ16 ተከታታይ ቀናት ሰነዱን በመግዛት በ17ኛው የሥራ ቀን ይከፈታል፡፡ ሰነዱን መግዛት የሚችሉት ከኢንተርፕራይዙ ዋና መ/ቤት ጎተራ አጎና ሠራዊት ሲኒማ አጠገብ ባለ ኬር ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 402 ሲሆነ የጨረታ ሰነድ መሸጫ ዋጋ የማይመለስ 200 ብር ሲሆን ሰነዱ የሚሰጠው በሶፍት ኮፒ ነው። ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያቸውን በታሸገ ፖስታ በማድረግ በተጠቀሰው ቀን ከጠዋቱ 2:30 እስከ 8:00 ሰዓት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በማስገባት በጨረታው እንዲትሳተፋ ተጋብዛችኋል፡ የጨረታ ሳጥኑ በዕለቱ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኢንተርፕራይዙ ዋና መ/ቤት ጎተራ አጎና ሠራዊት ሲኒማ አጠገብ ባለኬር ህንፃ /Baleker Tower/ 6ኛ ፎቅ በሚገኘው የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ቢሮ ቁጥር 603 ይከፈታል።
ኢንተርፕራይዙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ ማብራሪያ፡-
ስ.ቁ 011-466-25-27/011-416 03 09 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ
