የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የመስክ ሥራዎችን ለማከናወን ፎርክሊፍት፣ የሠራተኛ ሰርቪስ እና የከተማ ውስጥ ጭነት አገልግሎት የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
የፎርክሊፍት፣ የሠራተኛ ሰርቪስ፣ እና የከተማ ውስጥ ጭነት ተሽከርካሪ ኪራይ አገልግሎት ግዥ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር NEBE/NCB/03/2018
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የመስክ ሥራዎችን ለማከናወን ፎርክሊፍት፣ የሠራተኛ ሰርቪስ እና የከተማ ውስጥ ጭነት አገልግሎት የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሰረት፡- ሎት አንድ፡- የፎርክሊፍት
ሎት ሁለት፡- የሠራተኛ ሰርቪስ እና ፒካፕ
ሎት ሦስት፣- የከተማ ውስጥ ጭነት ተሽከርካሪ ኪራይ አገልግሎት ግዥ ለመፈፀም
- በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ጨረታው እስከሚዘጋበት ቀን ድረስ ባሉት የስራ ቀናት የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 300.00 /ሦስት መቶ ብር/ በመክፈል ከቦርዱ ግዥ ስራ ክፍል ቢሮ ቁጥር 107 ማግኘት ይችላሉ።
- በዘርፉ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ፣ ተጨማሪ እሴት ታክስና የግብር ከፋይ ምዝገባ ሠርተፍኬት፣ የዘመኑ ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ሠርተፍኬት እና በመንግስት ኤሌክትሮኒክስ ግዥ በአቅራቢነት የተመዘገቡ ስለመሆኑ የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ፤
- ተወዳዳሪዎች በሚወዳደሩበት መስክ ያላቸውን መልካም አፈጻጸም የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ከቦርዱ የግዥ አስተዳደር የሥራ ክፍል በመውሰድ ሞልተው አግባብ ካለው አካል በመፈረም ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለሎት አንድ ብር 10,000.00 (አስር ሺህ ብር) ለሎት ሁለት ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) ለሎት ሦስት ብር 30,000.00 (ሰላሳ ሺህ ብር) በባንከ የተረጋገጠ ዋስትና ወይም ሲፒአ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ተወዳዳሪዎች ቴክኒካል ፕሮፖዛል እና ፋይናንሻል ፕሮፖዛል በተለያየ ፖስታ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣
- ጨረታው ጥቅምት 04 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ተዘግቶ በዕለቱ ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፤
- ቦርዱ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፣
አድራሻችን፡- ቦሌ ፍላሚንጎ ካፌ ገባ ብሎ
ስልክ ቁጥር፡- +251 115153468
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
