የቴፒ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2018 በጀት አመት በቴፒ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ሳይቶች በግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ የሚከተሉትን የኮሪደር ልማት ስራ ለማሰራት ይፈልጋል።
የግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የቴፒ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2018 በጀት አመት በቴፒ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ሳይቶች በግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ የሚከተሉትን የኮሪደር ልማት ስራ ለማሰራት ይፈልጋል።
1/ኛ ከአቶ ያረጋል ሱቅ እስከ ሚሊንየም ጎዳና 346 ሜትር
2/ኛ ከኪዳነ ምህረት ክሊኒክ፤ ሚሊንየም ጎዳና እስከ ተካልኝ ልኳንዳ ቤት 564 ሜትር
3/ኛ ከሾሻ ጤና ጣቢያ እስከ ቴፒ ፖስታ ቤት ድረስ 1,020 ሜትር
4/ኛ ከአቢሲንያ ባንክ ቴሌ እስከ ንግድ ባንክ 380 ሜትር
5/ኛ ከእህት አማቾች ሆቴል እስከ ሚሊንየም መንገድ ድረስ 660 ሜትር
በዚሁም መሰረት GC-5/GENERAL CONTRARACTOR-5 ከዚህ በላይ የሆኑትን ተጫራቾችን በጨረታው እንዲሳተፋ ይጋብዛል። በዚሁም መሰረት በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች ለ2018 ዓ.ም የታደሰ ንግድ ፍቃድ ኮፒ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የግብር ከፋይነት የምስክር ወረቀት ኮፒ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የቫት (የተጨማሪ እሴት ታክስ) ተመዝጋቢ የሆኑበትን ኮፒ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የአቅራቢነት ሰርትፍኬት ኮፒ ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ከገቢዎች ጽ/ቤት በ2017 በጀት አመት ግብር ስለመክፈላቸው የሚገልጽ ከገቢዎች ጽ/ቤት ክሊራንስ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ጨረታውን ሲያቀርቡ ለጨረታ ማስከበርያ የሚሆን ብር 500,000 (አምስት መቶ ሺ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ጨረታውን ሲያሸንፉ ለጨረታ ውል ማስከበሪያ የሚሆን የጠቅላላ ዋጋው 10% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ አለባቸው።
- ተጫራቾች ዋጋ የተሞላበትን ፋይናንሻልና ቴክኒካል ሰነድ አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ በማድረግ በተለያየ ፖስታ በማድረግ በእለቱ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
- ተጫራቾች ዝርዝር የጨረታ ሰነዱን ቴ/ከ/ፋ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ግዥ ስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 42 በመቅረብ ብር 500 ብር በመክፈል መውሰድ ይችላሉ።
- ጨረታው በአየር ላይ የሚቆየው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ ለተከታታይ 21 ቀናት የሚቆይ ሲሆን ጨረታው በ22ኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 (አራት) ሰአት ላይ ታሽጎ ከቀኑ 8፡00 ሰአት ላይ የሚከፈት ይሆናል። በእለቱ በአል ወይም ዝግ ከሆነ በሚቀጥለው ስራ ቀን የሚከፈት ይሆናል። በእለቱ በጨረታው መክፈቻ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ካልተገኙ መስሪያ ቤቱ ጨረታውን የመክፈት መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች ከዚህ በፊት በአሰሪ መስሪያ ቤት፣ በዞኑ ውስጥም ሆነ በሌሎች አከባቢዎች ተመሳሳይ ስራ ወስደው ያስተጓጎሉ፣ ያቋረጡ፣ ያለበቂ ምክንያት ያዘገየ እንዲሁም ከአሰሪ መ/ቤትም ሆነ ተቆጣጣሪዎች በመሰል ተግባራት ማስጠንቀቂያ የተሰጠውና ቅጣት የተጣለበት ወይም ውል የተቋረጠበት ተጫራች በቀጥታ ከጨረታው ይወገዳል።
- መስሪያ ቤቱ የተሸለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ ማብራሪያ ቴ/ከ/ፋ/ጽ/ቤት ግዥ ፋ/ን/አር ስራ ሂደት በስልክ ቁጥር 0924286400/0913915370 በመደወል መጠየቅ ይቻላል።
የቴፒ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት
