የአርሲ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት ለአርሲ ዞን ቡሳ ጎነፋ ቅርንጫፍ የተለያዩ ጥሬ እህል በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ለሦስተኛ ግዜ የወጣ የግልፅ
ጨረታ ማስታወቂያ
የአርሲ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት ለአርሲ ዞን ቡሳ ጎነፋ ቅርንጫፍ የተለያዩ ጥሬ እህል በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ከዚህ ቀጥሎ የተመለከቱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ድርጅቶች እንዲወዳደሩ እንጋብዛለን፡፡
- ማንኛውም ድርጅቶች በጨረታው ላይ መካፈል ይችላሉ።
- ተጫራቾች ለጨረታው ማስከበሪያ ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ላይ 20 ፐርሰንት የያዘ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ በአርሲ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት ስም በማሠራት ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት የሥራ ቀን ጀምሮ ለ 15 ተከታታይ የሥራ ቀናት የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ከአርሲ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 106 በመግዛት ማስታወቂያ ከወጣበት በ16 ኛው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ሰነዱን ማስገባት የሚኖርባቸው ሲሆን ጨረታው በዚሁ ዕለት ከጥዋቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ዕለቱ በዓል ወይም ዝግ ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን ጨረታው ይከፈታል።
- ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0222381142 ደውለው ይጠይቁ፡፡
የአርሲ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት
