የኢትዮጵያ ፖስታ ከዚህ በታች በሎት የተጠቀሰውን አንጸባራቂ ፒፕስ በጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ግጨ 07/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ፖስታ ከዚህ በታች በሎት የተጠቀሰውን አንጸባራቂ ፒፕስ በጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል። ሠንጠረዥ 1 ግዥ የሚፈፀምበት የጨረታ አይነት
|
ተራ ቁጥር |
ሎት |
የጨረታ አይነት |
ብዛት |
ሰነዱ የሚመለስበት የመጨረሻው ቀን |
የመክፈቻ ቀን |
|
1 |
1 |
አንጸባራቂ ፒፕስ |
100 |
ጎዳር 10/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 6፡00 ሰዓት |
ጎዳር 10/2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡30 ላይ ይከፈታል |
ስለሆነም፡-
በዚህ ጨረታ ለመካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ከሆኑ ተጫራቾች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም በድርጅቱ ገንዘብ ቤት የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል ዋናው መ/ቤት 2ኛ ፎቅ ግዥ ክፍል እየቀረቡ የጨረታ ሠነድ በመውሰድ ለሎት 1 ቴክኒካልና ፋይናንሻል ሰነድ ለየብቻ (በተናጠል) በጨረታ ሠነዱ ላይ በዝርዝር በተገለጸው የሥራ ዝርዝር (Specification) መሠረት ዋጋ በመሙላት በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ እስከ ኅዳር 10 ቀን 2018 ዓ.ም 6፡00 ሰዓት ድረስ ሠነዱን ከገዙበት ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
❖ ለሎት 1 በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ ተመላሽ የሚሆን የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ (CPO) 30,000.00 (ሰላሳ ሺህ ብር) በማሠራት ከቴክኒካል ኦርጅናል ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታው ኤንቨሎፕ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ኅዳር 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት በድርጅቱ የሠራተኞች ክበብ ይከፈታል፡፡
CPO (ሲፒኦ) ሲያሠሩ ፡- የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት ወይም ETHIOPIAN POSTAL SERVICE ENTERPRISE በማለት ያሰሩ፡፡
ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- 0991187513/0918427568 /ደውለው መጠየቅ ይቻላል፡፡
