ድርጅታችን አያት አክሲዮን ማህበር የግንባታ ስራ በሚያከናውንባቸው ሳይቶች (አያት ዞን-2፣ አያት ዞን-3፣ ሃና ማርያም፣ አያት ዞን-8 እና ካዛንቺስ) የጥበቃ አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶችን በጨረታ አወዳድሮ የጥበቃ አገልግሎት ለመግዛት ይፈልጋል።
የጥበቃ አግልግሎት ግዥ ጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር፡-ASC/BID/0041/2018
ድርጅታችን አያት አክሲዮን ማህበር የግንባታ ስራ በሚያከናውንባቸው ሳይቶች (አያት ዞን-2፣ አያት ዞን-3፣ ሃና ማርያም፣ አያት ዞን-8 እና ካዛንቺስ) የጥበቃ አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶችን በጨረታ አወዳድሮ የጥበቃ አገልግሎት ለመግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ፡-
- ከላይ የተጠቀስውን አገልግሎት ለመስጠት ፍላጎት፤ ብቃት እና ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው ተጫራቾች ከመገናኛ ወደ ካራ በሚወስደው መንገድ ወሰን ሚካኤል ትራፊክ መብራት አጠገብ በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት ግዥ መመሪያ ሦስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 311 ድረስ በመቅረብ ከጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የተዘጋጅውን የጨረታ ሠነድ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል እስከ ህዳር 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መግዛት ይቻላሉ።
- በጨረታው ለማሣተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች
- በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፤ የግብር ከፋይ እና ቫት ሰርተፍኬት ኮፒ፣
- የዘመኑ ግብር ስለመክፈሉ የሚያረጋገጥ ወቅታዊ ደብዳቤ ከአገር ውስጥ ገቢ፣
- ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተሰጠ የሥራ ፈቃድ
- በፌደራል ፖሊስ የተሰጠ የብቃት ማረጋገጫ እንዲሁም፤ በኮንስትራክሽን ድርጅት የተሰጠ የጥበቃ አገልግሎት/ልምድ፣ ከሚወደደሩበት የዋጋ ማቅረቢያ ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) በሲፒኦ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ባልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በአያት አክሲዮን ማህበር ስም አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
- ተጨራቾች የሚወደደሩበትን ዋጋ በጨረታ ሠነዱ ላይ በተዘጋጀው የዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ ወይም ተመሳሳይ ይዘት ባለው ፎርም ላይ በመሙላት እስከ ህዳር 2 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ለዚሁ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ገቢ በማድረግ በጨረታው መሣተፍ ይችላሉ። ጨረታው በተዘጋበት ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአክሲዮን ማህበሩ ዋናው መስሪያ ቤት ይከፈታል።
- የጨረታ አሸናፊ የሆኑ የጥበቃ አገልግሎት ሰጭዎች አሽናፊነታችው በተገለፀላችው በ7 ቀናት ውስጥ በጨረታ ሰንዱ ውስጥ የተገለፀውን የውል ማስከበሪያ በማስያዝ ለዚሁ የተዘጋጀውን ውል መፈረም ይጠበቅባቸዋል። ይህ ካልሆነ ለጨረታ ማስረከቢያ ያስያዙት ገንዘብ ለድርጅቱ ገቢ ይደረጋል።
- አክሲዮን ማህበሩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ስልክ ቁጥር +251-115514699/+251-116463445
አያት አክሲዮን ማህበር
