የሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በ2018 በጀት ዓመት ኮርፖሬሽኑ ለሥራ የሚፈልጋቸውን ሎት 1. የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች እና ካሜራ አክሰሰሮች ሎት 2 Server በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በ2018 በጀት ዓመት ኮርፖሬሽኑ ለሥራ የሚፈልጋቸውን ሎት 1. የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች እና ካሜራ አክሰሰሮች ሎት 2 Server በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በመሆኑም በዚህ ጨረታ መወዳደር የሚችሉ
- ህጋዊ የንግድ ምዝገባ ፍቃድ ያላቸው
- በመስኩ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያላቸው
- የቫት ተመዝጋቢነት ሰርተፍኬት ያላቸው
- በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ያላቸው ድርጅቶች ሀዋሳ ወንዶ ንግድ ኩባንያ ህንጻ ጀርባ በሚገኘው በኮርፖሬሽኑ ህንጻ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 202 በአካል መምጣት የተዘጋጀውን ጨረታ ሰነድ ለእያንዳንዱ ጨረታ የማይመለስ ብር 500 በመክፈል መግዛት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለኤሌክትሮኒክስ 10,000 ብር እንዲሁም ለServer 5000 ብር በባንክ በተረጋገጠ CPO ብቻ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- የጨረታውን የመወዳደሪያ ዋጋ ኮርፖሬሽኑ ባዘጋጀው ሰነድ ላይ በመሙላት ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ ሥራ ቀናት ውስጥ የመወዳደሪያ ፖስታዎችን ቴክኒካል ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ እንዲሁም ፋይናንሻል ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ እያንዳንዳቸውን ለየብቻ በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ በማድረግ በአንድ ትልቅ ፖስታ በማሸግ ለዚህ በተዘጋጀው ጨረታ ሳጥን ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታውም በ11ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ4፡30 ሰዓት የሚከፈት ሲሆን ቀኑ የዕረፍት ቀን ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ ቀን በተመሳሳይ ቦታና ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። መሥሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0916037261 ደውሎ መጠየቅ የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን።
የሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን
