በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሀ/ማርያምቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የፅህፈት መሳሪያ፣ የኢሌክትሮኒክስ ማስተማሪያ እቃ፣ የኮንስትራክሽን ማስተማሪያ፣ የዕዳት እቃ፣ የማሽን ትምህርት ማስተማሪያ እቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሀ/ማርያምቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የፅህፈት መሳሪያ፣ የኤሌክትሮኒክስ ማስተማሪያ እቃ፣ የኮንስትራክሽን ማስተማሪያ፣ የፅዳት እቃ፣ የማሽን ትምህርት ማስተማሪያ እቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል።
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው
- የዘመኑ ግብር የከፈሉ ስለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
- የግዥው መጠን ብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸውና የታደሰ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ 1-4 የተጠቀሱትን የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው
- ተጫራቾች በጨረታ ሰነድ ላይ የሚሞሉት የነጠላ ዋጋ ምንም አይነት ስርዝ ድልዝ እንዲኖርበት አይፈቀድም። ስርዝ ድልዝ ያለበትና የማይነበብ ከሆነ ከጨረታው ውጭ ይደረጋል። በጠቅላላ ዋጋው ላይ ስህተት ቢያጋጥምም እንኳን የመጀመሪያውን አሀዝ ለመለየት በሚያስችል መልኩ አንድ ስርዝ ብቻ ሰረዝ በማድረግ የተስተካከለውን አሀዝ ከጎኑ መፃፍ ፓራፍ ፈርማ ማድረግ ይኖርባቸዋል።
- የሚገዙ እቃዎች አይነት ዝርዝር መግለጫ /እስፔስፍኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ከግ/ፋ/ደ/የስራ ሂደት ከፍል ቢሮ ቁጥር-04-ማግኝት ይቻላል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድቦንድ/ ለሚወዳደሩበት አገልግሎቱን ጠቅላላ ዋጋ 1% በባንክ በተረጋገጠ ክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ መሂ 1 በመቁረጥ የመሂ 1 ኮፒ ተደርጎ ማያያዝ አለባቸው።
- ጨረታው በአየር ላይ የሚቆየው ለ15 ተከታታይ ቀናት ሲሆን ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሣቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ ሆኖ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጂ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፓስታ በሀ/ማ/ቴ/ሙ ማ/ኮሌጅ በግ/ፋ/ደ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 04 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በጋዜጣ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ 16ኛ ቀን ከቀኑ 4፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ/ፋ/ን/አስ/ደ/የሥራ ሂደት በቢሮ ቁጥር 04 በ16ኛው ቀን ከቀኑ 4፡15 ታሽጎ በዛው ቀን ከቀኑ 4፡30 ይከፈታል። 16ኛው ቀን በዓል ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከቀኑ 4፡15 ታሽጎ በዚያው ቀን ከቀኑ 4፡30 ይከፈታል።
- በተጫራቾች መመሪያ ላይ የተጠየቁ ናሙናዎች ካሉ ጨረታው ከመከፈቱ ቢያንስ 3ቀን አስቀድሞ ማቅረብ አለባቸው።
- የጨረታው አሸናፊ የሚሆን አቅራቢ ያሸነፈውን እቃዎች ሙሉ በሙሉ በወቅቱ ለሀ/ማ/ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ በሚገኘው ንብረት ክፍል መጋዘን ድረስ አምጥቶ የማስረከብ ግዴታ አለበት።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈለጉ ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 04 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 0116190056 ወይም 0116190179 በመደወል ማግኝት ይችላሉ።
አድራሻ አማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሀ/ማ/ከ/ወ/ ሾላ ገበያ ቴ/ሙ/ኮሌጅ ሾላገበያ ርቀት ከአ.አ 130 እና ከደ/ብርሃን 82 ኪ.ሜ ሲሆን ለማንኛውም ተሽከርካሪዎች ምቹ የሆነ መንገድ ነው
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ሥራና ሥልጠና ቢሮ የሀገረ ማርያም ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ
