በአብክመ የከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታል ለ2019 በጀት ዓመት ለተለያዩ አገልግሎት የሚውሉ አላቂ የቢሮ መገልገያ እቃዎች ፣የፅህፈት መሳሪዎች የመኪና መለዋወጫ እና ጌጣጌጦች እቃዎች፣የፅዳት እቃዎች ደንብ ልብስ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡ ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ ፍቃደኛ የሆኑ፡-
የብሔራዊ ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
በአብክመ የከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታል ለ2019 በጀት ዓመት ለተለያዩ አገልግሎት የሚውሉ አላቂ የቢሮ መገልገያ እቃዎች ፣የፅህፈት መሳሪዎች የመኪና መለዋወጫ እና ጌጣጌጦች እቃዎች፣የፅዳት እቃዎች ደንብ ልብስ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡ ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ ፍቃደኛ የሆኑ፡-
1. በዘርፉ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው ፤ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ፤ለስራው የምዝገባ የምስክር ወረቀት ያላቸውና የግብር ከፋይ መለያ /IN/ያላቸው፡፡
2. የጨረታው ሰነድ ከከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታል ቢሮ ቁጥር 50 በግዥ/ፋ/ንብ/አስ/የስራ ሂደት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ከላይየተዘረዘሩትን መረጃዎች ዘውትር በስራ ቀንና ሰዓት ለእያንዳንዱ ሰነድ የማይመለስ የኢትዮ.ብር 500/አምስት መቶ ብር ብቻ /በመከፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡
3. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋናና ኮፒ በማድረግ በታሸገ ኤንቨሎፕ በአብክመ ከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታል በግዥ/ፋይ/ንብ/አስ/የስራ ሂደት ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ አስራ ስድስተኛዉ/16/ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 4፡00 ሰዓት ድረስ ባለው ጊዜ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
4. ጨረታው በአስራ ስድስተኛው ቀን 4፡01 ሰዓት ተዘግቶ 4፡30 ሰዓት ላይ በግዥ ፋይ/ንብ/አስ/የስራ ሂደት ቢሮ ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡የመከፈቻ እለቱ የበዓል ወይም የእረፍት ቀን ከሆነ በሚቀጥለዉ የስራ ቀን ከላይ በተጠቀሰዉ ሰዓት ይከፈታል፡፡
5. ተጫራቾች ተመላሽ የሚደረግ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ላይ2% /ከሁለት ፐርሰንት/በጥሬ ገንዘብ ወይንም በባንከ ትእዛዝ/CPO/ማስያዝ አለባቸው::
6. የጨረታ አሸናፊ የሆነው ድርጅት ውል በሚዋዋልበት ጊዜ የውለታ ማስከበሪያ ከአጠቃላይ ድምር ዋጋ 10% ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
7. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
8. የዕቃው ርክክብ ቦታ በከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታል ይሆናል፡፡
9. ውድድሩ በነጠላ ዋጋ የምንወስድ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
10. ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታል በግንባር በመቅረብ ወይንም በስልክ ቁጥር +251972847872 ደውለው መረዳት ይችላሉ፡፡
በአብክመ የከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታል
