በቾ ወሊሶ የገበሬዎች ሕብረት ስራ ዩኒየን የተለያየ ዓይነት ያገለገሉ እና አዲስ የፋብሪካ ማሽኖች እና የተለያዩ አይነት ያገለገሉ ኮምፒውተሮች በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል::
ለ3ኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
በቾ ወሊሶ የገበሬዎች ሕብረት ስራ ዩኒየን የተለያየ ዓይነት ያገለገሉ እና አዲስ የፋብሪካ ማሽኖች እና የተለያዩ አይነት ያገለገሉ ኮምፒውተሮች በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል:: በመሆኑም መግዛት የሚፈልግ ግለሰብ ወይም ድርጅት ከዚህ ቀጥሎ ያሉትን መስፈርቶች በማሟላት ተወዳድሮ መግዛት ይችላል::
ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው፡-
1. ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው እና የአመቱን ግብር የከፈሉ እንዲሁም የተጨማሪ እሴት ታከስ ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል::
2. ለጨረታ ሰነድ ግዢ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት) በዩኒየኑ የባንክ ሂሳብ ቁጥር
1000087184327 ኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንከ ወይም የኢትዮጵያ ንግድ ባንከ
1000036818348 በመከፈል ሰነዱን ከዩኒየን መውሰድ አለባቸው::
3. ለጨረታ ማስረከቢያ ቢድ ቦንድ ማስያዣ ያቀረቡትን ዋጋ 5% በሲፒኦ ወይም በባንክዋስትና ሰነድ ማስያዝ አለባቸው::
4. ተጫራች የጨረታ ሰነዶቹን በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ 19/03/2018ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ ዘወትር በሥራ ሰዓት ዩኒየኑ ባዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይችላሉ::
5. የጨረታ መክፈቻ ቀን 19/03/2018 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል::
6. ተጫራቾች አንዱ ተጫራች ባቀረበው ዋጋ ላይ ተንተርሰው ዋጋ ማቅረብ የተከለከለ ነው::
7. ዩኒየኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
8. አሸናፊው ተጫራች ያሸነፈውን ንብረት ሙሉ በሙሉ እስከ 10 ቀን ጊዜ ውስጥ ማንሳት ይኖርበታል::
አድራሻ፡- በጅማ መንገድ ከአዲስ አበባ 80ኪ.ሜ ቱሉ ቦሎ ከተማ ላይ እንገኛለን::
ለተጨማሪ ማብራሪያ፡- በስልከ ቁጥር 0911080003/0912122971 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል::
የበቾ ወሊሶ የገበሬዎች ሕብረት ስራ ዩኒየን
