ለሸካ ዞን ማሻ ማረሚያ ተቋም በስሩ ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች ቀለብ እህል፣ ጥራጥሬ እና ሸቀጣሸቀጥና ጽ/መሳሪያ ከታህሳስ 1/2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 30/2018 ዓ.ም ለ120 ቀናት ከሚያቀርቡ ህጋዊ ፍቃድ ካላቸው ድርጅቶች /አቅራብ ነጋዴዎችና ማህበራት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ለሸካ ዞን ማሻ ማረሚያ ተቋም በስሩ ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች ቀለብ እህል፣ ጥራጥሬ እና ሸቀጣሸቀጥና ጽ/መሳሪያ ከታህሳስ 1/2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 30/2018 ዓ.ም ለ120 ቀናት ከሚያቀርቡ ህጋዊ ፍቃድ ካላቸው ድርጅቶች /አቅራብ ነጋዴዎችና ማህበራት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚሁ መሠረት ተጫራቾች ሟሟላት የሚገባቸው ግዴታዎች፡-
1ኛ/ በየዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የታደሰ የዘመኑን ንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
2ኛ/ ተጨማሪ ዕሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ
3ኛ/ የጨረታው ተወዳዳሪዎች ለእህል ጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000 /ሃምሳ ሺህ/ ብር እና ለሸቀጣሸቀጥ ብር 20,000 /ሃያ ሺህ /ብር ጥሬ /በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ በማስያዝ የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 በመክፈል ከቢሮ ቁጥር 3 የጨረታ ሰነድን መግዛት የሚችል።
4ኛ/ ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ በሰም በታሸገ ፖስታ በማድረግ ፊርማና የድርጅቱን ማህተም ያለውን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ለዚሁ ጨረታ አገልግሎት በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
5ኛ/ ጨረታው በ16ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በ8፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች ብገኙም ባይገኙም ይከፈታል።
6ኛ/ ጨረታ የሚከፈትበት ቀን የመንግስት ሥራ ሰዓት ካልሆነ በሚቀጥለው ቀን በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት ይከፈታል።
7ኛ/ የጨረታው አሸናፍ የሆነው አቅራብ ዕቃዎችን አጓጉዞ በራሱ ወጭ ለማሻማ/ተቋም ማስረከብ የሚችል።
8ኛ/ ተጫራቾች አሁን ባቀረቡት ዋጋ ለ4 ተከታታይ ወር ማቅረብ የሚችል ሲሆን በመሀሉ የድርድር ጥያቄ ተቀባይነት የለውም።
9ኛ/ ተጫራቾች የውል ማስከበሪያ 10% ለማስያዝ ፈታደኛ የሆነ።
10 / ተቋሙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፍል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
የሸካ ዞን ማሻ ማረሚያ ተቋም
