Tender Detail

Tender Details


የደቡብ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በሎት አንድ ለተለያዩ ቀላልና ከባድ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት የሚውል የተለያየ መጠን ያላቸውን ባትሪዎች ብቁ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት እና በሎት ሁለት ደግሞ በሥሩ ላሉት ዲስትሪክቶች አገልግሎት የሚውሉ የኮንስትራክሽን እና ኢንጅነሪንግ መሣሪያዎች መገልገያ ማለትም ዶዘር፣ ግሬደር፣ ኤክስካቫተር፣ሮለር እና ሎደር በድጋሚ ብቁ ተጫራቾችን አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል።


የባትሪ ግዥ እና የማሽነሪ ደግሞ በድጋሚ ኪራይ አገልግሎት ለመፈፀም የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ

 

ደኢመባ ቁጥር 04/2018

የደቡብ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በሎት አንድ ለተለያዩ ቀላልና ከባድ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት የሚውል የተለያየ መጠን ያላቸውን ባትሪዎች ብቁ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት እና በሎት ሁለት ደግሞ በሥሩ ላሉት ዲስትሪክቶች አገልግሎት የሚውሉ የኮንስትራክሽን እና ኢንጅነሪንግ መሣሪያዎች መገልገያ ማለትም ዶዘር፣ ግሬደር፣ ኤክስካቫተር፣ሮለር እና ሎደር በድጋሚ ብቁ ተጫራቾችን አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል።

 በመሆኑም፡-

  1. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን የዘመኑን ግብር የተከፈለበትን ከሚፈለገው አገልግሎት የተዛመደ የንግድ ሥራ ወይም የአገልግሎት ሥራ ፈቃድ ከሁለት መቶ ሺህ ብር በላይ ላለቸው ግዢዎች የቫት ተመዝጋቢ ሥለመሆናቸው ማስረጃ በአቅራቢነት የተመዘገቡ መሆናቸው የምዝገባ ማስረጃ እና በጨረታ ለመሳተፍ ከሚመለከተው የመንግስት አካል የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  2. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሀሳብ የሚያቀርቡበትን የጨረታ ሰነድ የቴክኒክ እና ፋይናንሻሉን አንድ ኦሪጅናል እና ሁለት ኮፒ በማድረግ ለየብቻው በታሽገ ፖስታ የጨረታ ማስከበሪያው ደግሞ ኦሪጅናልና ኮፒ በተለየ ፖስታ በማድረግ ስማቸውን፣ ፊርማቸውን፣ አድራሻቸውንና የሚጫረቱበትን የጨረታ ዓይነት በትክክል ማስፈር አለባቸው።
  3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ለየአንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 400.00 /አራት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል ከባለስልጣኑ ዋና ቢሮ ቁጥርመውሰድ ይችላሉ።
  4. አቅራቢዎች ጨረታውን ለዚህ ተግባር በተዘጋጀ ሳጥን ገቢ የሚያደርጉበት ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን ከቀኑ 800 ድረስ ይሆናል። ጨረታው በዚያኑ ቀን ከቀኑ 830 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል። ዕለቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል።
  5. ተጫራቾች በእንግሊዘኛ የተጻፈውን የቴክኒክ ዝርዝር መግለጫ በሚጠይቀው መሠረት መሙላት ይጠበቅባቸዋል። ይህንን ያልሞሉት የቴክኒክ ዝርዝር መግለጫ እንዳልቀረበ ተቆጥሮ የማቅረብያ ሰነዱ ውድቅ ይደረጋል።
  6. ተጫራቾች ለሎት ሁለት ለእያንዳንዱ ማሽን ብር 50.000.00 /ሃምሳ ሺህ ብር/ እና ለሎት አንድ ደግሞ ከዚህ በታች በቀረበው መሠረት

.

 

የዕቃው ዓይነት

 

Capacity (AH)

 

Qty

 

የጨረታ ማስከበሪያ

 

1

 

Lead-Acid Battery

 

70 Amp

 

20

 

5,000.00

 

2

 

Lead-Acid Battery

 

75 Amp

 

20

 

13,500.00

 

3

 

Lead-Acid Battery

 

210 Amp

 

14

 

1,200.00

 

4

 

Lead-Acid Battery

 

150 Amp

 

75

 

35,000.00

 

5

 

Lead-Acid Battery

 

120 Amp

 

08

 

3,500.00

 

6

 

Lead-Acid Battery

 

90 Amp

 

20

 

4,000.00

 

 

የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ/ሲፒኦ/ ወይም በባንክ ዋስትና ወይም ከኢንሹራስ ዋስትና በቀር በግዥ መመሪያው ላይ ባሉ አማራጮች በፈለጉት ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

  1. ጨረታው ከተከፈተ በኃላ ተጫራቾች ባቀረቡት የጨረታ ሰነድ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግ አይችሉም።
  2. ጨረታውን ለማዛባት የሚሞክሩ ተጫራቾች ከጨረታው ይሰረዛሉ። ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ይወረሳሉ፡፡ ለወደፊቱም /ቤቱ በሚያወጣው የግዥ ጨረታ እንዳይሳተፉ ይደረጋል።
  1. ተጫራቾች ያቀረቡት ዋጋ ጨረታው ከተከፈተ በኃላ 45 ቀናት ፀንቶ መቆየት አለበት።
  2. ለሎት አንድ የጨረታው አሸናፊ ድርጅት መሆኑ ከተገለፀለት አምስት /5/ ቀናት ውስጥ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ዋስትና /Performance Bond/ 10% በባንክ ጋራንቲ ወይም በሲፒኦ በማቅረብ ውል መፈረም ይኖርበታል፤ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ውል ለመፈረም ፈቃደኛ ያልሆነ ተጫራች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው የጨረታ ማስከበሪያ ይወረሳል።

ለበለጠ መረጃ ተጫራቾች የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ፦

የደቡብ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን

ግዥና ንብረት አስተዳደር ኬዝ ቲም

የፖሳቁ

የስልክ ቁጥር 046 131 5012/ 09 23 69 00 85

ፋክስ

ዲላ ኢትዮጵያ

የደቡብ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን

 

 

Save Tender