በኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የአቃቂ ቤዚክ ሜታል ኢንዱስትሪ የDouble Column Plano Machine, Bronze Fumace 0.5 ton እና Small Boring machine አስጠግኖ ወደ ስራ ለማስገባት በአገር ውስጥ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የግዥ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በኢትዮ ኢንጂንግ ግሩፕ
የአቃቂ ቤዚክ ሜታል ኢንዱስትሪ
የጨረታ ቁጥር:አቤሜኢ /ሰቼማ/ግጨ/2018/04
በኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የአቃቂ ቤዚክ ሜታል ኢንዱስትሪ የDouble Column Plano Machine, Bronze Fumace 0.5 ton እና Small Boring machine አስጠግኖ ወደ ስራ ለማስገባት በአገር ውስጥ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
- በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የግብር መክፈያ ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥና በግብር ሰብሳቢ ባለሥልጣን የተሰጠ ማስረጃ ቅጂ፣ አግባብ ያለው በዘርፋ የታደሰ ንግድ ስራ ፍቃድ ቅጂውን፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰርተፍኬት እና የግብር መከፈያ መለያ ሰርተፍኬት ከመጫረቻ ሰነድ ጋር ማቅረብ አለባቸው።
- የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 300.00 /ሦስት መቶ ብር/ በአቃቂ ቤዚክ ሜታልስ ኢንዱስትሪ ስም ሒሳብ ቁጥር 1000014630906 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገቢ በማድረግ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከሰኞ- አርብ ጠዋት 2፡00-6:00 ሰዓት ከሰዓት 7:00-11፡00 ሰዓት ኢንዱስትሪያችን ቀጥር ግቢ በመቅረብ ሰነዱን ከግዥ ክፍል መግዛት ይችላሉ።
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺ ብር) በCPO ወይም bank guarantee ወይም Cash ቢያንስ ለ88 ቀናት ፀንቶ የሚቆይ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- ጨረታው በጋዜጣ ከታተመበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የስራ ቀናት አየር ላይ የሚቆይ ሆኖ በ16ኛው ቀን 8፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዚሁ እለት በ8:15 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 1ኛ ወለል ግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 22 ውስጥ ይከፈታል።
- ጨረታው ከሚከፈትበት ቀን ጀምሮ ለ60 ቀናት ፀንቶ ይቆያል።
- ሲንዱስትሪው ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ቴክኒካልና ፋይናንሻል ለየብቻ ሆኖ በኢንቨሎፕ አሽጐ ዋናውና ኮፒውን ለየብቻ በማድረግ በተዘጋጀው ግዥ ሳጥን ውስጥ ማስገባት፤
አድራሻ፡- ከአ/አ ወደ ዱከም መሄጃ መንገድ ላይ ከሚገኘው ሸገር ከተማ የፍተሻ ጣቢያ (ኬላ) አጠገብ ከASTCO FOOD COMPLEX በቀኝ በኩል ሁለት መቶ ሜትር ገባ ብሎ ይገኛል።
ለተጨማሪ መረጃ :- ስልክ ቁጥር 011 434 04 09/ 011 435 06 08
በኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ አቃቂ ቤዚክ ሜታልስ ኢንዱስትሪ
