በአዲስ አበባ ቃሊቲ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በፍ/ቤት ትዕዛዝ በኢስተርን ኢንዱስትሪ ዞን (ዱከም) የሚገኝ የፋብሪካ ማሸነሪዎችና ዕቃዎችን ማለትም Used Fully electric socks knitter machine፣ Used computerized knitter (fully computerized socks knitting machine)፣ Used 3 Phase electronic voltage stabilizer (voltage regulator)፣ Used screw compressor እና Used Refrigeration compressed air drier ባሉበት ሁኔታ በግልዕ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
በጉምሩክ ኮሚሽን አ.አ ቃሊቲ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በፍ/ቤት ትዕዛዝ መሠረት ለሽያጭ
የቀረቡ የፋብሪካ ማሽነሪዎችና ዕቃዎች ሽያጭ ማስታወቂያ ቁጥር 28/2018
በአዲስ አበባ ቃሊቲ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በፍ/ቤት ትዕዛዝ በኢስተርን ኢንዱስትሪ ዞን (ዱከም) የሚገኝ የፋብሪካ ማሸነሪዎችና ዕቃዎችን ማለትም Used Fully electric socks knitter machine፣ Used computerized knitter (fully computerized socks knitting machine)፣ Used 3 Phase electronic voltage stabilizer (voltage regulator)፣ Used screw compressor እና Used Refrigeration compressed air drier ባሉበት ሁኔታ በግልዕ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ከዚህ በታች በቅፁ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ለጨረታ የሚቀርቡ ንብረቶች ዝርዝር መረጃ ተዘጋጅቶ ከሀሙስ ህዳር 25 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለተጫራቾች በሚቀርብ የጨረታ ሰነድ ላይ የሚታወቅ መሆኑን እንገልጻለን።
በመሆኑም፡-
- በግልጽ ጨረታ በቀረቡት ዕቃዎች ላይ ለመወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች በዘርፉ የፀና የንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ ስለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መሥሪያ ቤት የተሰጠ ማስረጃ ሰነዶች ኮፒ እና የጨረታ ማስከበሪያ ቼክ ወይም (CPO) ከመጫረቻ ሰነዱ ጋር አያይዞ በኤንቨሎፕ ወይም በፖስታ በማሸግ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል።
- በጨረታው ላይ የዕቃው አስመጪ ወይም ባለቤትና ቤተሰቡ የነበሩ ሰዎች መሣተፍ አይችሉም።
- ተጫራቾች የዕቃዎቹን ጨረታ ሰነድ ከሀሙስ ህዳር 25 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ) በመክፈል በቅ/ጽ/ቤቱ በመገኘት የጨረታ ሠነዱን መግዛት ይችላሉ።
- በዕቃ ግልፅ ጨረታ ለመሳተፍ ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው ዕቃዎች የሰጡትን ዋጋ አምስት በመቶ (5%) ለጨረታ ማስከበሪያ ቼክ (CPO) በቅ/ፅ/ቤቱ አድራሻ ስም፡- CUSTOMS COMMISSION ADDIS ABABA KALITY CUSTOMS BRANCH OFFICE በባንክ አሰርተው ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ ቀናት (ስኬጁል) መሰረት መጫረት ይችላሉ።
|
ተ.ቁ |
የቅ/ጽ/ቤቱ ስም |
የጨረታው አይነት |
የንብረት መመልከቻ ቀን የጨረታ ሰነድ ከወሰዱ ቀን ጀምሮ |
የጨረታው የመዝጊያ እና የመክፈቻ ቀንና ሰዓት |
|
1 |
አ.አ ቃሊቲ ጉምሩክ ቅ/ፅ/ቤት |
የእቃ ግልፅ |
እስከ 01/04/2018 |
02/04/2018 3:45 ተዘግቶ በዚያውኑ ቀን 4፡00 ሰዓት ይከፈታል |
- የጨረታው መክፈቻ ቦታ፡- አአ ቃሊቲ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት (ናይል ኢንሹራንስ ህንጻ) የሚካሄድ ሲሆን ጨረታው ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ወይም በታዛቢዎች ፊት ይከፈታል፡፡
- ተሸናፊ ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ያስያዙት (CPO) የጨረታው ውጤት በተገለፀ በ3 የስራ ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል።
- አሸናፊ ተጫራቾች ማሸነፋቸውን ከተገለፀላቸው ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ገንዘብ ገቢ በማድረግ ዕቃውን ማንሣት ይኖርባቸዋል። አሸናፊ ተጫራቾ የገዙትን ዕቃ በራሳቸው ወጪ ከፋብሪካው የማንሳት፣ የመጫንና የማጓጓዝ ግዴታ ይኖርባቸዋል።
- ከላይ በተ/ቁ 8 በተገለፁት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረክቦ ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበርያ ያስያዙት እና ለንብረቱ የከፈሉት ዋጋ ለቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሚ ለሽያጭ ይቀርባል።
- መ/ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በስልከ ቁጥር፡- አዲስ አበባ ቃሊት ጉምሩክ፡- 011 – 470 – 85 – 03
ማሳሰቢያ፡- ዕቃዎቹን ኢስተርን ኢንዱስትሪ ዞን (ዱከም) በአካል በመሄድ መመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
የጨረታ ሰነድ መሸጫ አድራሻ፡- ሳሪስ አቦ ቤ/ክ በቀለበት መንገድ ወደ ማሰልጠኛ በሚወስደው መንገድ ኖክ ማደያ ያለበት አዲሱ ህንጻ ገንዘብ ያዥ ቢሮ
በአዲስ አበባ ቃሊቲ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት
