የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ከመንግሥት በተመደበ ገንዘብ የዓይናማ ተመሪዎችን መማሪያ እና ማስተማሪያ መጽሐፍ ለዓይነስውራን ተማሪዎች መማሪያና ማስተማሪያ እንዲሆን የማስማማት (Adaptation) ወደ ብሬል የመቀየር፤ የማሳተም እና አጓጉዞ በከልሉ በሚገኙ አምስት የከዘና ማዕከላት የማስረከ ሥራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር EB/EMAS/013/2018
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ከመንግሥት በተመደበ ገንዘብ የዓይናማ ተመሪዎችን መማሪያ እና ማስተማሪያ መጽሐፍ ለዓይነስውራን ተማሪዎች መማሪያና ማስተማሪያ እንዲሆን የማስማማት (Adaptation) ወደ ብሬል የመቀየር፤ የማሳተም እና አጓጉዞ በከልሉ በሚገኙ አምስት የከዘና ማዕከላት የማስረከብ ሥራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
1. የዘመኑ የታደሰ ሀጋዊና በዘርፉ አግባብነት ያለው የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው!
3. የተጨማሪ እሴት ታከስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስከር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
4. የዓይናማ ተማሪዎችን መማሪያ እና ማስተማሪያ መጽሐፍ ለዓይነስውራን መማሪያና ማስተማሪያ እንዲሆን የማስማማት (Adaptaion)፣ ወደ ብሬል የመቀየር፣ የማሳተም እና ወደ ከዘና ማዕከላት የማጓጓዝ ሥራ አይነትና ቴከኒካል የፍላጎት ዝርዝር መግለጫ (Specifcation) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 600.00 /ስድስት መቶ ብር/ በመከፈል ቢሮ ቁጥር 103 ማግኘት ይችላሉ፡፡
6. ተጫራቶች የዓይናማ ተመሪዎችን መማሪያ እና ማስተማሪያ መጽሐፍ ለዓይነስውራን ተማሪዎች መማሪያና ማስተማሪያ እንዲሆን የማስማማት (Adaptation)፣ ወደ ብሬል (በመቀየር፣ የማሳተም እና አጓጉዞ ለማስረከብ የሚያቀርቡት የጨረታ ማስከበሪያ ብር 500,000.00 /አምስት መቶ ሺህ ብር/ ሲሆን ይህም በባንከ በተረጋገጠ የከፍያ ትዕዛዝ (ሰ.ፒ.ኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
7. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሐሳቡን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ትምህርት ቢሮ በትምህርት ግብዓት ጥናትና አቅርቦት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 103 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ጨረታው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 16 ቀናት ውስጥ ማስገባት የሚቻል ሲሆን በ16ኛው ቀን የጨረታ ሰነድ ማስገባት የሚቻለው እስከ ጥዋቱ 4፡00 ድረስ ብቻ ይሆናል፡፡
8. ጨረታው የሚከፈተው ጨረታው አየር ላይ በዋለ በ16ኛው ቀን ሲሆን ካላንደር የሚዘጋው በዓል፣ ቅዳሜና እሑድ ቀን ከሆነ ቀጥሎ ባለው የስራ ቀን የጨረታ ሳጥኑ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በትምህርት ቢሮ የስብሰባ አዳራሽ 4፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡
9. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
10. በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ቢሮ ቁጥር 103 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 0583205654 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ
