በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ሸዋ ዞን የኤ/ግ/ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በአውሮፓ ህብረት እና በአማራ ክልል አደጋ ስጋት ቅነሳ ሥራ አመራር ኮሚሽን ያልተማከለ አደጋ ስጋት በጀት በፈረድ ውሃ ናዘሮ ቁጥር 2 ካናል ማራዘም አነስተኛ መስኖ ግንባታ ሥራ እና በካራለጎማ ቀበሌ የምንጭ ማጎልበት ሥራ እና ማስፋፊያ በጨረታ አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል፡፡
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር ኤግገ/09/289/2018
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ሸዋ ዞን የኤ/ግ/ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በአውሮፓ ህብረት እና በአማራ ክልል አደጋ ስጋት ቅነሳ ሥራ አመራር ኮሚሽን ያልተማከለ አደጋ ስጋት በጀት በፈረድ ውሃ ናዘሮ ቁጥር 2 ካናል ማራዘም አነስተኛ መስኖ ግንባታ ሥራ እና በካራለጎማ ቀበሌ የምንጭ ማጎልበት ሥራ እና ማስፋፊያ በጨረታ አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም መወዳደር የምትፈልጉ፡-
- በዘርፉ የተመዘገበ እና በዘመኑ የታደሰ የንግድ ሥራ ፍቃድ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የግዥ መጠኑ ብር 200,000 እና ከዚህ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት መረጃ ማቅረብ የሚችል፤
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለካናል ሥራ 100,000 ብር ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ጀምሮ ለ120 ቀን የሚቆይ /ለምንጭ ማጎልበት ሥራ 10,000 ብር እና ከዚያ በላይ ማሲያዝ እንደሚጠበቅባቸውና ይኸውም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ በጽ/ቤታችን ገቢ ደረሰኝ በመቁረጥ ኮፒ በማድረግ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብራችሁ ማስገባት ይኖርባችኋል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ መክፈቻ ወቅት እንዲገኙ አይገደዱም ነገር ግን በጨረታው መገኘት አለብን ብለው ካሰቡ መገኘት ያለበት አካል የተጫረተው ባለቤት ወይም ህጋዊ ውከልና ያለው አካል ኦርጅናል የውክልና ማስረጃውን ይዞ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከኤ/ግ/ወረዳ ገንዘብ ጽቤት ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 21 ተከታታይ ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት ከቢሮ ቁጥር 6 መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ጨረታው በአየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ማለትም ከ03/04/2018 እስከ 23/04/2018 ለ21 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሆኖ በ22ኛው ቀን ማለትም ከ24/04/2018 ከጠዋቱ 3፡30 ታሽጎ 4፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግ እና ከጨረታው እራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
- ተጫራቾች ለወሰዱት የተጫራቾች መመሪያ /የጨረታ ሠነድ/ በእያንዳንዱ ገፅ ላይ የድርጅታቸውን ማህተም በማድረግ መመለስ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
- በዚህ ማስታወቂያ ያልተገለፁ ነገር ግን በጨረታው ወሳኝ የሆኑ መስፈርቶች እና መረጃዎች በግዥ መመሪያ መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች በዋጋ መሙያ ሰነዱ ላይ ስርዝ ድልዝ ማድረግ የማይፈቀድ ሲሆን ስርዝ ያለበት ሰነድ ከውድድር ውጭ ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች ለካናል ሥራ/ WWC ደረጃ 5 እና ከዚያ በላይ የሆነ የምስክር ወረቀት የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ ማስረጃ፤ በዘመኑ የግብር ክሊራንስ ማቅረብ አለባቸው ለምንጭ ማጎልበት ሥራ WWC ደረጃ 6 እና በላይ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ማስረጃ፣ የዘመኑ የግብር ከሊራንስ ኮፒ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራች ካናል ሥራ የቴክኒካል ፖስታ እና የፋይናንሺያል ፖስታ ለየብቻው ማድረግ ይጠቅባቸዋል።
ማሳሰቢያ፡- ጨረታው የሚከፈትበትን የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ሸዋ ዞን የኤ/ግ/ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
