አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴያትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ፍላሚንጎ አካባቢ አዲስ ባስገነባው የህፃናትና ወጣቶች ቴአትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስ በላይኛው እና በታችኛው በር እንዲሁም ፒያሳ በሚገኘው ሃገር ፍቅር ቴያትር ቤት በሚገኘው በር በጠቅላላ ለ3 በር ለመኪና ማቆሚያ (Parking) የሚሆን የመኪና መግቢያና መውጫ መቆጣጠሪያ ማሽን ከነገጠማው እንዲሁም የማስተዳደር ስራውን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 001/2018
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴያትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ፍላሚንጎ አካባቢ አዲስ ባስገነባው የህፃናትና ወጣቶች ቴአትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስ በላይኛው እና በታችኛው በር እንዲሁም ፒያሳ በሚገኘው ሃገር ፍቅር ቴያትር ቤት በሚገኘው በር በጠቅላላ ለ3 በር ለመኪና ማቆሚያ (Parking) የሚሆን የመኪና መግቢያና መውጫ መቆጣጠሪያ ማሽን ከነገጠማው እንዲሁም የማስተዳደር ስራውን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርት የምታሟሉ ህጋዊ ተጫራቾች የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ) ብቻ ጥሬ ገንዘብ በመክፈል ሰነዱን አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴያትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ፍላሚንጎ አካባቢ አዲስ ባስገነባው የህፃናትና ወጣቶች ቴአትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስ ህንጻ አንደኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 1-06 ግዥና ንብረት አስተዳደር ቢሮ መውሰድ ትችላላችሁ።
- የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችል እና የዘመኑን ግብር የከፈለ።
- በዘርፉ የተሰማሩበት ንግድ ፍቃድ ማቅረብ አለባቸው።
- አቅራቢነት የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል።
- የቫት ተመዝጋቢ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል።
- በዘርፉ በቂ ልምድ ያለውና ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ ቫትን ጨምሮ በገዙት ሰነድ ላይ ባለው የዋጋ ማቅረቢያ ቦታ በግልጽ ማሰፈርና መጨረሻ ቦታ ላይ ፊርማና ወህተም በመምታት አንድ ኦርጅናል እና አንድ ኮፒ ለየብቻ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ለዚህ ተግባር በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- የጨረታ ማስከበሪያ ብር 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ብቻ ከመወዳደሪያ ፖስታ ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት የጨረታ ሰነዱን ማስጠባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው በ11ኛው ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ተዘግቶ ከሰዓት በኋላ 7፡30 ሰዓት ተጫራቾቹ ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ነገር ግን የመክፈቻ ቀኑ የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ከላይ በተገለጸው ሰዓት የሚከፈት ይሆናል።
- ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡-
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴያትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ፍላሚንጎ አካባቢ አዲስ ባስገነባው የህፃናትና ወጣቶች ቴአትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስ አንደኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 1-06 ግዥና ንብረት አስተዳደር ቢሮ።
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 0911924597
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት
