ሪች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ መንግስታዊ ያልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን ከፕላን ኢንተርሽናል እና ዩኒሴፍ በተገኘ የበጀት ድጋፍ በበጀት ዓመቱ እቅድ መሰረት ለህጻናት መማሪያ የሚሆን ሞንቶሶሪ ኪት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የመጨረሻ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
ሪች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ መንግስታዊ ያልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን ከፕላን ኢንተርሽናል እና ዩኒሴፍ በተገኘ የበጀት ድጋፍ በበጀት ዓመቱ እቅድ መሰረት ለህጻናት መማሪያ የሚሆን ሞንቶሶሪ ኪት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ
|
የዕቃው አይነት
|
መለኪያ
|
ብዛት
|
ምርመራ/ አስተያየት
|
|
1
|
ሞንቶሶሪ ኪት (ከ4 እስከ 6 ዓመት ላሉ ህጻናት የሚሆን ሙሉ ፓኬጅ የያዘ)
|
በቁጥር
|
14
|
ሙሉ አምስት ፓኬጅ
|
በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ቢያንስ የሚከተሉትን ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
- የዘመኑ የታደሰ የንግድና የታደሰ የዋና ምዝገባ ፈቃዳቸውን፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ሰርተፍኬት፣ በጨረታ እንድትሳተፉ ለዘመኑ በጀት ዓመት ብቻ የሚያገለግል የምስክር ወረቀት እና ቲን ሰርተፍኬት ፎቶ ኮፒውን በማያያዝ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ሰባት የሥራ ቀናት ውስጥ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከ2፡30 – 6፡30 እና ከሰዓት 7፡30 – 11፡30 ከላይ የተዘረዘሩትን መረጃዎች ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን በማያያዝ ዲላ በሚገኘው ሪች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ ጽ/ቤት ሂሳብ ክፍል በመምጣት መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒውን በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ (ፖስታ) የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ 2% ሲፒኦ በሪች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ ስም ተሰርቶ በኦርጅናል የጨረታ ሰነድ ውስጥ በማያያዝ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ከሰባተኛው/7ኛው/ ቀን በኋላ ባለው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 6፡30 ድረስ ለዚህ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታው በዕለቱ ከሰዓት 8፡00 ሰዓት ዲላ ሪች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ አዳራሽ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ፡- በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 046-331-0049/046-331-3145 ዘወትር በሥራ ሰዓት ደውሎ መጠየቅና መረዳት ይቻላል።
አድራሻ ፡- ሪች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ ዲላ ከተማ ከዲላይት ኢንተርናሽናል ሆቴል 100ሜትር ገባ ብሎ።
ሪች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ
