የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ለትምህርት ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ የሚኒሚዲያ ቁሳቁስ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር EB/EMAS/07/2018
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ለትምህርት ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ የሚኒሚዲያ ቁሳቁስ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፤ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር እንዲችሉ ተጋብዘዋል፡፡
- ዘመኑ የታደሰ ህጋዊና አግባብነት ያለው የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸዉ፤
- የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸዉን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር አያይዘዉ ማቅረብ አለባቸው፡፡ እነዚህን ሰነዶች አሟልቶ ያልቀረበ ተጫራች በውድድሩ ሊሳተፍ አይችልም፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 400.00 /አራት መቶ ብር/ በመክፈል ሰነዱን 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 103 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ብር 400,000.00 /አራት መቶ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ የከፍያ ትእዛዝ (ሰ.ፒ.አ.) (CPO) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም ጥሬ ገንዘብ በቢሮው ደረሰኝ ገቢ በማድረግ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ትምህርት ቢሮ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር103 በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ጨረታዉ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 16 ቀናት ውስጥ እስከ ጠዋቱ 4:00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታዉ የሚከፈተዉ ጨረታው አየር ላይ በዋለ በ16ኛው ቀን ሲሆን ካላንደር የሚዘጋው በዓል፣ ቅዳሜና እሁድ ቀን ከሆነ ቀጥሎ ባለዉ የስራ ቀን የጨረታ ሳጥኑ በ4:00 ሰዓት ተዘግቶ ተጫራቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በትምህርት ቢሮ የስብስባ አዳራሽ 4:30 ሰዓት ይከፈታል ።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
- በጨረታ መሳተፍ ለሚፈልጉ ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ቢሮ ቁጥር 103 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በፋክስ ቁጥር 058220 100 በመላክ ወይም በስልክ ቁጥር 0582201666/0583205654 በመደወል ማግኘት ይችላሉ።
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ
ባህርዳር
